top of page

ታህሳስ 17፣ 2015- የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አባ ፍራንሲስ ዓለማችን ሰላም እርቧታል አሉ

  • sheger1021fm
  • Dec 26, 2022
  • 1 min read

የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አባ ፍራንሲስ ዓለማችን ሰላም እርቧታል አሉ፡፡


ዓለማችን ሰላምን ተርባለች ያሉት የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ባስተላለፉት መልዕክት እንደሆነ ዘ ኢንዲፔንደንት ፅፏል፡፡


ትርጉም አልባ ሲሉ የጠሩትም የዩክሬይኑ ጦርነት እንዲቆም ጠይቀዋል አባ ፍራንሲስ፡፡


ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ መልዕክት አብዛኛው ክፍል የዩክሬይኑን ጦርነት የተመለከተ ነው ተብሏል፡፡


አባ ፍራንሲስ በአለም ዙሪያ ግጭት በሚስተዋልባቸው ቦታዎች የሚንገላቱ እና በብዙ የተቸገሩ ሰዎችንም እንዳሰቧቸው በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


በአለም ዙሪያ ግጭት እና ጦርነት እንዲያበቃ መማፀናቸው ተሰምቷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page