top of page

ታህሳስ 17፣ 2015- በአሜሪካ በከባዱ የክረምት ቅዝቃዜ ምክንያት የ38 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰማ

  • sheger1021fm
  • Dec 26, 2022
  • 1 min read

በአሜሪካ በከባዱ የክረምት ቅዝቃዜ ምክንያት የ38 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰማ፡፡


በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ እና ካናዳ ከባድ ቅዝቃዜ መከሰቱን ዘ ግሎብ ኤንድ ሜይል ፅፏል፡፡


በዚሁ መጥፎ የአየር ሁኔታ ምክንያት በካናዳም 4 ሰዎች መሞታቸው ተሰምቷል፡፡


ቅዝቃዜው በበረዷማ ውሽንፍር የታጀበ ነው ተብሏል፡፡


በዚሁ መጥፎ የአየር ሁኔታ ምክንያት በአሜሪካ በሺህዎች የሚቆጠሩ የአውሮፕላን በረራዎች መሰረዛቸው ታውቋል፡፡


በአሜሪካም ሆነ በካናዳ የኤሌክትሪክ መጥፋት ያስከተለባቸው ቦታዎች እንዳሉ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page