top of page

ታህሳስ 14፣2017 - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ በቅርቡ ይፋ ያደረገው ዝቅተኛ የደሞዝ ጣሪያ አምራቾች አካባቢ አነጋጋሪ እየሆነ መምጣቱን ሰምተናል

  • sheger1021fm
  • Dec 23, 2024
  • 1 min read

በጋርመንትና መሰል ስራ የሚሰማራ ባለሙያ በደሞዝ ክፍያ ብቻ ቀጥሮ ማሰራት አዋጭ አይደለም የሚሉት በዘርፉ የተሰማሩ ባለሃብቶች እስካሁን እየተደረገ የነበረው ከደሞዝ በተጨማሪ ሰራተኛው በሰራው ስራ ልክ ከደሞዙ በተጨማሪ ክፍያ እንዲያገኝ እናደርግ ነበር ብለዋል፡፡

ይህ አሰራር ለባለሃብቱም ለሰራተኛውም ጠቃሚ ነው የሚሉት ባለሃብቱ አሁን የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የጀመረው አሰራር ግን ጉዳቱ ለአምራቾች ከፍ ያለ ነው ሲሉ ነግረውናል፡፡

የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ከተማ አስተዳደሩ ያወጣው ዝቅተኛ የደሞዝ ጣሪያ አካሄዱህጋዊነት ጥያቄ ቢኖርበትም ዝቅተኛ ደሞዝ ጣሪያ መወሰን ግን አለበት በዚህ ላይ እስማማለሁ ብሏል፡፡

ይህ ችግር እስከወዲያኛው የሚፈታው ወጥ በሆነ መንገድ እንደ ሀገር ዝቅተኛ የደሞዝ ጣሪያ ይፋ ሲደረግ ነው ብሏል፡፡

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በበኩሉ በማህበራዊ ትስስር ገፅ ላይ ባወጣው መረጃ ዝቅተኛ የደመወዝ ጣርያ አስቀመጠ በሚል የሚሰራጭብኝ  ዘገባ የተሳሳተ ነው ሲል መግለጫ ሰጥቶ የነበረ ሲሆን በዚሁ ዘገባው ማጠቃልያ ላይ ደግሞ ዝቅተኛ ደሞዝ ጣሪያ ለግብር ከፋዮች አስቀምጦ እያስከፈለ መሆኑን ይጠቅሳል፡፡

በረከት አካሉ



 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page