top of page

ታህሳስ 13፣ 2015- የጋምቢያ መንግስት የተሴረብኝን ወታደራዊ ግልበጣ አከሸፍኩት አለ

  • sheger1021fm
  • Dec 22, 2022
  • 1 min read

የጋምቢያ መንግስት የተሴረብኝን ወታደራዊ ግልበጣ አከሸፍኩት አለ፡፡


የመንግስት ግልበጣ ሞካሪዎቹ በደፈናው ወታደሮቸ ናቸው ከመባሉ ውጭ ዝርዝሩ አልተጠቀሰም፡፡


ስለ ግልበጣው ከገለልተኛ ወገኖች በኩል የተሰማ አስተያየት እንደሌለ ዴይሊ ትረስ ፅፏል፡፡


አራት ወታደሮች ከመንግስት ግልበጣ ሴራው ጋር በተገናኘ ተይዘው መታሰራቸው ተሰምቷል፡፡


የጋምቢያው ፕሬዝዳንት አዳም ባሮው በድጋሚ የተመረጡት ከአመት በፊት ነው፡፡


ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በምዕራብ አፍሪካ አገሮች የመንግስት ግልበጣዎች ሲደረጉ ቆይተዋል፡፡


ጊኒ፣ ማሊ እና ቡርኪናፋሶ የመንግስት ግልበጣ የተደረገባቸው አገሮች ናቸው፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page