top of page

ታህሳስ 12፣ 2015- በአፍጋኒስታን የታሊባኖች አስተዳደር በአገሪቱ ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ሴቶች እንዳይማሩ ከለከለ

  • sheger1021fm
  • Dec 21, 2022
  • 1 min read

በአፍጋኒስታን የታሊባኖች አስተዳደር በአገሪቱ ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ሴቶች እንዳይማሩ ከለከለ፡፡


ክልከላው ያለ ምንም መዘግየት በአገሪቱ በሚገኙ ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ስራ ላይ እንደሚውል የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትሩ መናገራቸው ሻይን ድረ ገፅ ፅፏል፡፡


ባለፈው አመት ሴት ልጆች በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዳይማሩ መከልከላቸው ዘገባው አስታውሷል፡፡


የአሁኑ እርምጃ የአፍጋኒስታን ሴት የከፍተኛ ተቋማት ተማሪዎችን በእጅጉ እያሳዘነ ነው ተብሏል፡፡


ሴቶቹ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ውሳኔው የወደፊት ተስፋችንን አጨልሞብናል ማለታቸው ተሰምቷል፡፡


ጉዳዩ በአለም አቀፍ ደረጃም ውግዘት እየገጠመው ነው ተብሏል፡፡


የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአፍጋኒስታን ሴቶች በዩኒቨርስቲዎች እንዳይማሩ መከልከላቸውን በፅኑ አውግዞታል ተብሏል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page