top of page

ታህሳስ 11፣2017 - ‘’ከታህሳስ 9/2017 ጀምሮ እየቀነሰ የመጣው ቅዝቃዜ በመጪዎቹ 10 ቀናት ጨርሶ እየጠፋ ይሄዳል’’

  • sheger1021fm
  • Dec 20, 2024
  • 1 min read

ባሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያን እና ሌሎች የአለም ክፍሎችን ያዳረሰው የሳይቤሪያ ቅዝቃዜ ከትናንት ጀምሮ እየቀነሰ እንደሆነ የብሔራዊ ሜትዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተናገረ፡፡


የኢንስቲትዩቱ የሜትዮሮሎጂ ትንበያና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ምርምር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አሳምነው ተሾመ (ዶ/ር) ሌሊትና ንጋት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ ይስተዋል የነበረው ከሳይቤሪያ ተነስቶ ኢትዮጵያንና ሌሎች የአለም ክፍሎችን ያዳረሰው #ቅዝቃዜ እየቀነሰ መሆኑን ነግረውናል፡፡


በሳለፍነው ሳምንት በደቡብ ትግራይ፣ በምስራቅ አማራ፣ በመካከለኛው ኢትዮጵያ፣ አዲስ አበባን ጨምሮ በሰሜን ሸዋ ፍቼ እንዲሁም ሐረርና ጅግጅጋ ከፍተኛ ቅዝቃዜ ተስተናግዷል ብለዋል፡፡


‘’ከታህሳስ 9/2017 ጀምሮ እየቀነሰ የመጣው ቅዝቃዜ በመጪዎቹ 10 ቀናት ጨርሶ እየጠፋ ይሄዳል’’ ብለዋል ዶ/ር አሳምነው፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…

ወንድሙ ሀይሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page