top of page

ታህሳስ 11፣2017 - አማራ ባንክ "አባ QR Code " በሚል ስያሜ ያዘጋጀውን መተግበሪያ አገልግሎት አስጀመረ

  • Dec 20, 2024
  • 1 min read

አማራ ባንክ "አባ QR Code " በሚል ስያሜ ያዘጋጀውን መተግበሪያ አገልግሎት አስጀመረ።


መተግበሪያው ተገልጋዮች ማንኛውንም አይነት ግብይት ሲፈጽሙ የእጅ ስልካቸውን ብቻ በመጠቀም በየግብይት ማዕከሉ የሚገኘውን የነጋዴውን QR Code ያለ ጥሬ ገንዘብ ከማንኛውም የባንክ ሂሳባቸው ወይም የሞባይል ባንክ መተግበሪያ ክፍያ መፈፀም የሚችሉበት መሆኑ ተነግሯል።


በአባ ኪው አር ደንበኞች ለግብይት ወይም ለተጠቀሙት አገልግሎት ለነጋዴው የተዘጋጀውን የፈጣን ምላሽ አሻራ በእጅ ስልካቸው ቅኝት ሲያደርጉ ወዲያውኑ የገዙትን እቃ ወይም አገልግሎት አይነት፣ ዝርዝር፣ ብዛት እንዲሁም ዋጋ በስልካቸው ማየት እንዲችሉ ያደርጋል ሲሉ የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዩሀንስ አያሌው(ዶ/ር) ተናግረዋል።


ነጋዴዎች ደግሞ በአማራ ባንክ ፈጣን ምላሽ መተግበሪያ አማካኝነት ምርትና አገልግሎታቸውን የዋጋ ማሻሻያ፣ ተጨማሪ የአቅርቦት ዝርዝር ወይም ሌሎች አገልግሎቶችን ለማካተት ቢፈልጉ በማንኛውም ጊዜ ማስተካከያ ማድረግ ይችላሉ ተብሎለታል።

#አማራ_ባንክ ትናንት ወደ ስራ ያስገባውን ጨምሮ ሌሎች የዲጅታል የባንክ አገልግሎት ለደንበኞች ለማድረስ እየሰራ መሆኑን የተናገሩት ዋና ስራ አስፈፃሚው በቅርቡም የዲጅታል ብድር አገልግሎ ተጠቃሽ ነው ብለዋል።


የባንኩ ሞባይል መተግበሪያ ደንበኞች ክፍያን መፈፀም፣ ገንዘብ ማስተላለፍ፣ የአየር ትኬት መቁረጥ፣ የውሃ ክፍያ መፈፀምን ጨምሮ ደንበኞች ግብር የሚከፍሉበትን ስርዓት አቅርቤያለሁ ብሏል።


ባንኩ የዲጅታል ባንክ አገልግሎትን የበለጠ ለማስፋት ከኢትዮ ቴሌኮም፣ ከሳፋሪኮም፣ ከብሔራዊ ስዊች፣ ከፋይናንስ ቴክኖሎጂ አቅራቢዎች፣ ከክፍያ አመቻቾች እና እንደ ገቢዎች ሚኒስቴር ካሉ መንግስታዊ ተቋማት ጋር እየሰራሁ ነው ብሏል።


ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Recent Posts

See All
የነሐሴ 4 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሳውዲ_አረቢያ በሳውዲ አረቢያ ጂዛን በሚገኝ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ከባድ ቃጠሎ ተቅስቅሶ ነበር ተባለ፡፡ በጂዛኑ ማጣሪያ ላይ ቃጠሎ ተቅስቅሶ የነበረው ከባድ ፍንዳታ ከተሰማ በኋላ እንደሆነ አናዶሉ ፅፏል፡፡ በጁቢየል የተፈጥሮ ጋዝ ማሰናጃ ከተማም ቃጠሎ ተቀስቅሶ ነበር ተብሏል፡፡ የሳውዲ ምንጮች ቃጠሎዎቹ ተቀስቅሰው እ

 
 
 
በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡

ነሐሴ 4 2018 በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት በበኩሉ ሳያጠፋ የምንቀጣው አሽከርካሪ የለም እንዲያውም ሁሉንም ህጎች እናስከብር ብንል የማይቀጣ አሽከርካሪ አይኖርም ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.... ምህረት ስዩም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page