top of page

ታህሳስ 11፣2017 - ''በዓላት መዳረሻ ወቅት የሸቀጦች የዋጋ መናር እንዳይኖር ባዛሮችን አሰናድቼ እየጠበቅኳችሁ ነው'' የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ

  • sheger1021fm
  • Dec 20, 2024
  • 1 min read

የበዓላት መዳረሻ ወቅት በአዲስ አበባ ከተማ የሚፈጠረውን የምርት እጥረት እና የሸቀጦች የዋጋ መናር እንዳይኖር ከዚህ ቀደም እንደማደርገው ባዛሮችን አሰናድቼ እየጠበቅኳችሁ ነው ሲል የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ተናገረ፡፡


ለመጪው ገና በዓልም #አምራቾች ወደ ከተማዋ መጥተው ከሸማቹ ጋር በቀጥታ የሚገናኙበትን መንገድ አመቻችቻለሁ ብሏል፡፡


በዚህም መውጫ በሮች ላይ የከተማ አስተዳደሩ ባዘጋጃቸው 4ቱም የገበያ ማዕከላት (ኮልፌ፣ አቃቂ፣ ለሚ ኩራ እና ላፍቶ) ምርቶችን በብዛትም በቅናሽም ታገኛላችሁ ያሉት የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ፍስሐ ጥበቡ ከላፍቶ የገበያ ማዕከል በስተቀር በሌሎቹ የገበያ ማዕከላት የአትክልት እና የሰብል ምርት እየቀረበ ነው ብለዋል፡፡

ሸማቾች ላፍቶ #የገበያ_ማዕከል ብትሄዱ ደግሞ አትክልት እና የፍራፍሬ ምርቶችን ነው የምታገኙት ሲሉ ምክትል ሀላፊው ተናግሯል፡፡


የቅዳሜ እና እሁድ ገበያም 3 ዓመት ያለፈው መሆኑን የተናገሩት አቶ ፍስሀ 197 የሚሆኑ ማዕከላት ስላሉ እዚያ በመሄድ መሸመት ትችላላችሁ ብለዋል፡፡


የገና በዓል መዳረሻ ወቅት ላይ ቀናቶች ሲቀሩት በ14 ቦታዎች ባዛሮችን አዘጋጃለሁ ያለው ቢሮው በባዛሩም አምራቾች፣ ኢንዱስትሪዎች እና አርሶ አደሮች ምርታቸው ቀጥታ አምጥተው ከሸማቹ ጋር የሚገናኙበትን መንገድ ዘርግቻለሁ ብሏል፡፡


ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page