top of page

ታህሳስ 11፣2017 - በኢነርጂ ፍጆታ እና በልዩ ልዩ ክፍያዎች ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ ተደረገ

  • sheger1021fm
  • Dec 20, 2024
  • 1 min read

በኢነርጂ ፍጆታ እና በልዩ ልዩ ክፍያዎች ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ፡፡


ከ200 ኪሎ ዋት ሰዓት በላይ በሚጠቀሙ ደንበኞች የፍጆታ ሂሳብ ላይ እና አዲስ ደንበኛ ማገናኘትን ጨምሮ ደንበኞች በሚፈፅሟቸው ልዩ ልዩ የአገልግሎት ክፍያዎች ላይ የ #ተጨማሪ_እሴት_ታክስ ተግባራዊ መደረጉን በላከልን መግለጫ ተናግሯል፡፡


በዚህ መሠረት ደንበኞች ወርሃዊ የፍጆታ ሂሳብ በሚከፍሉበት ወቅት የፍጆታ መጠናቸው ከ200 ኪሎ ዋት ሰዓት በላይ ከሆነ እላፊ የመጣው የፍጆታ መጠን የተጨማሪ እሴት ታክስ ተሰልቶ ሂሳባቸው ላይ የሚደመር ይሆናል ብሏል፡፡


ተቋሙ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ ያደረገው ከህዳር ወር የክፍያ ደረሰኝ ጀምሮ ሲሆን፤ የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች ከመስከረም ወር ጀምሮ ያለባቸውን የኋላ ክፍያ በታህሳስ ወር በሚወጣው #ቢል ላይ ተጨምሮ የሚከፍሉ ይሆናል ተብሏል፡፡


በተመሳሳይ የቅድመ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኖችም ከመስከረም ወር ጀምሮ ባላቸው የፍጆታ መጠን መሠረት የኋላ ክፍያ በቀጣይ ይከፍላሉ፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ደንበኞች ለተቋማችን በሚከፍሉት ልዩ ልዩ ክፍያዎች ላይም ተግባራዊ የሚደረግ ነው፡፡


በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ( #ኢቢሲ )ን የቴሌቭዥን አገልግሎት ክፍያ በወርሃዊ በደንበኞች የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ ላይ በመጨመር እንዲከፍሉ ሲያደርግ መቆየቱን ተቋሙ አስታውሷል፡፡


በመሆኑም ወርሀዊ የኤሌክትሪክ የፍጆታ መጠናቸው ከ50 ኪሎ ዋት ሰዓት በላይ የሆኑ ደንበኞች 10 ብር ከወርሃዊ ኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ ጋር የቴሌቪዥን አገልግሎት ክፍያ እየከፈሉ ይገኛሉ ሲል በመግለጫው አካቷል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page