ታህሳስ 11፣2017 - በቀደሙት ጊዜአት የኢትዮጵያ ሥርዓተ ትምህርት ክፍተት እንዳለበት ሲነገር ቆይቷል፡፡
- sheger1021fm
- Dec 20, 2024
- 1 min read
በቀደሙት ጊዜአት የኢትዮጵያ ሥርዓተ ትምህርት ክፍተት እንዳለበት ሲነገር ቆይቷል፡፡
ከዚህ ቀደም ዘርፉ እያስተናገደ ነው የሚባለውን ችግር ይፈታል የተባለ አዲስ ስርዓተ ትምህርት ተቀርፆ ወደ ትግበራ ገብቷል፡፡
በ2015 ዓ.ም ቅድመ አንደኛ ተማሪዎች ላይ ሙሉ ለሙሉ ወደ ትግበራ ሲገባ 1ኛ እና 2ተኛ ደረጃ ላይ ደግሞ በሙከራ ደረጃ ሲተገበር እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡
ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ሙሉ በሙሉ ወደ ትግበራ ገብቶ የመማር ማስተማሩ ቀጥሎ ቆይቷል፡፡
ሁለት ዓመታትን ያስቆጠረው አዲሱ #ሥርዓተ_ትምህርት ከቀደመው ሥርዓተ ትምህርት ቀየር ያደረጋቸው ለውጦች አሉ፡፡
ከእነዛም መካከል የ7ተኛ እና 8ተኛ ክፍል Biology, Chemistry እና Physics ከዚህ ቀደም በተናጥል ሲሰጡ የነበሩ የትምህርት ዓይነቶች በአንድ ተደርገዋል፡፡
በተጨማሪም የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ብቻ እንዲማሩ መደረጉ እና ግብረ ገብ የተሰኘ የትምህርት ዓይነት በትምህርት ሥርዓቱ መካተቱ ከለውጦቹ መካከል ናቸው፡፡
በዚህ ሂደት ውስጥም ሸገር ራዲዮ በተለያዩ ጊዜያት ያነጋገራቸው የትምህርት ባለሙያዎች አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት በተወሰነ መልኩ ሊስተካል ይገባል፤ የሚወጣው ወጥቶ መካተት የሚያስፈልገው መካተት አለበት ሲሉ ይደመጣል፡፡
ሁለት ዓመታትን ያስቆጠረው ይሄው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ምን ዓይነት በጎ ጎን አለው? ሂደቱስ ምን ይመስላል?
በታሰበው ልክ መሻሻሎች ይመጣሉ ተብሎ ተስፋ ይጣልበታለው ወይ የሚሉ እና ሌሎች ተያያዥ ጥያቄዎችን ለሰላሳ ዓመታት በትምህርት ዘርፉ ላይ የቆዩትን አቶ ተስፋዬ ለጋን ጠይቀናቸዋል፡፡
ፋሲካ ሙሉወርቅ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q
📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
Comments