top of page

ታህሣስ 1፣2017 - ምርጫ ቦርድ ከዚህ ቀደም እግድ ጥሎባቸው ከነበሩ ፖርቲዎች መካከል የአምስቱን እግድ ማንሳቱን ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Dec 10, 2024
  • 1 min read

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከዚህ ቀደም እግድ ጥሎባቸው ከነበሩ ፖርቲዎች መካከል የአምስቱን እግድ ማንሳቱን ተናገረ፡፡


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም 11 ፓርቲዎች ላይ የዕግድ ውሣኔ አስተላልፎባቸው እንደነበረ የታወሳል፡፡


ፓርቲዎቹ እግድ ተላልፎባቸው የነበረው፤ ከጠቅላላ ጉባዔ፣ ከኦዲትና በሴት አባላት ቁጥር አማካኝነት ከሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ ጋር በተገናኘ ነበረ፡፡


በወቅቱ እግድ ከተጣለባቸው 11 ፓርቲዎች አሁን ላይ የአምስቱ ዕግድ አንስቻለሁ ብሏል ቦርዱ፡፡


ፓርቲዎቹ እግዱ የተነሳላቸው የይቅርታና የመከላከያ መልስ በማቅረባቸው ነው ተብሏል፡፡


ምርጫ ቦርድ ዛሬ እግዳቸውን አንስቼላቸዋለሁ ያላቸው ፓርቲዎች፤


1. የዎላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ (ዎ.ብ.ን)፣


2. አዲስ ትውልድ ፓርቲ (አ.ት.ፓ)፣


3. የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጋ.ህ.ዴ.ን)፣


4. የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ህብረት (ኢ.ዴ.ህ) እና


5. የአገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ናቸው፡፡


ፓርቲዎቹ ያለፈውን ስህተት እንደማይደግሙና በቀጣይም የቦርዱን ሥራ ከሚያደናቅፍና ዕምነት ጥያቄ ውስጥ ከሚከቱ ተግባራት ተቆጥበው እንዲቆጠቡ በማሳሰብና በማስጠንቀቅ ዕግዱን ማንሳቱን ተናግሯል፡፡


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም እግድ ጥሎባቸው የነበሩና አሁን እግዱ ተነስቶላቸዋለሁ ከተባሉት ዝርዝር ውስጥ የሌሉት ፓርቲዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡


1. የኦሮሞ ነጻነት ንቅናቄ፣


2. አንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፖርቲ፣


3. ጌዲኦ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት፣


4. የሐረሪ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት፣


5. የገዳ ሥራዓት ለኦሮሞ ነጻነት ፓርቲ እና


6. የጋምቤላ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ናቸው።


ማንያዘዋል ጌታሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page