በ2018 በጀት ዓመት 9 ወራት 103 አዲስ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ፡፡
- May 4
- 1 min read
ሚያዝያ 26/2018
በ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት 103 አዲስ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ፡፡
አገልግሎቱ ከዋናው ግሪድና ከግሪድ የራቁ በርካታ አዳዲስ አካባቢዎችን ተጠቃሚ ማድረጉን እና ከጤናና ማህበራዊ ተቋማት በተጨማሪ ከ31 ሺህ በላይ አባዎራዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግሯል፡፡
በዚህም 82ቱ ከዋናው የኤሌክትሪክ መረብ (ግሪድ) እንዲሁም 21 የገጠር ከተሞችና መንደሮችን ደግሞ በፀሃይ ኃይል አማራጭ (ኦፍግሪድ) የተገናኙ መሆናቸውን ሰምተናል፡፡

በተጨማሪም 423,200 አዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ያለ ሲሆን ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ18 ነጥብ 6 በመቶ ብልጫ አለው ተብሏል፡፡
ኃይል ከተገናኘላቸው አዳዲስ ደንበኞች ውስጥ 31 ሺህ 298 ያህሉ አዲስ የኤሌክትሪክ ተደራሽ በሆኑት የገጠር ከተሞችና መንደሮች ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድቷል፡፡
አዲስ ኤሌክትሪክ ካገኙ ደንበኞች መካከል 74.2 ከመቶ የድህረ ክፍያ እንዲሁም 25 ነጥብ 8 በመቶ የቅድመ ክፍያ ቆጣሪ ተጠቃሚ ናቸው፡፡
በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ ደንበኞች ቁጥር 5.64 ሚሊዮን ደርሷል መባሉን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያገኘነው መረጃ ያሳያል ፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments