top of page

‘’በእስር ላይ ያሉ ሰዎችን ለመፍታት፣ በጫካ እና በውጭ ያሉትን ደግሞ በይቅርታ ለማስገባት ልባችን ሰፊ መሆን ይኖርበታል" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

  • Jul 7
  • 1 min read

ሰኔ 30/2018


"የመንግስት ሀላፊዎችና ፖለቲከኞች የሀይማኖት አባቶችንና ትላልቅ ሰዎችን ተጠቅመን በተቻለ መጠን በእስር ላይ ያሉ ሰዎችን ለመፍታት፣ በጫካ እና በውጭ ያሉትን ደግሞ በይቅርታ ለማስገባት ልባችን ሰፊ መሆን ይኖርበታል" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ።


ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በፓርላማ በነበራቸው ቆይታ ማጠቃለያ ላይ ይህንን ማድረግ የሚያስፈልገው ለኢትዮጵያ ሲባል ነው ብለዋል።


“TPLF 'ም ጭምር ቀልብ ከገዛ፣ አእምሮ ከገዛ ለመነጋገርና ሰላም ለማምጣት ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል” ሲሉም አስረድተዋል።


“ከሰላም ሙከራ ውጪ ያለው አይጠቅመንም፣የሚያስፈልገን ብልፅግና ላማት ነው” ብለዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ያለፉትን አምስት አመታት በፓርላማ የቆዩ የተፎካካሪ ፖርቲ አባላት ሀሳባቸውን በግልፅ ያቀረቡ እንደራሴዎችንም አመስግነዋል።


"የተፎካካሪ ፓርቲ አባላት፣በምክር ቤት የነበራችሁ ብርቱ ሰዎ፣ ሀሳባችሁን በግልፅ ለመናገር የደፈራችሁ ፣በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የሞከራችሁ፣ሃሳባችሁ ምንም ይሁን ምን በግልፀኝነት ለማቅረብ የሞከራችሁ ጀግኖች ናችሁ፣ ለኢትዮጵያ ዲሞክራሲ የማይናቅ ሚና ተጫውታችኋልና እናመሰግናችኋለን" ብለዋል።


ፓርላማ ብቻ አይደለም የትብብር መስክ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "ልባችሁንና አዕምሯችሁን ከፍታችሁ በተለይ ደግሞ በኮሪደር ላይ አብረን እንድንሰራ አደራ ማለት እፈልጋለሁ" ብለው ጥሪ አቅርበዋል።


የብልጽግና አባል የሆኑም ያልሆኑም የምክር ቤት አባላትን በምክር ቤቱ ኢትዮጵያን ስላገለገሉ “ኢትዮጵያም መንግሥታችንም አብዝቶ ያመሰግናችኋል” ሲሉም ተናግረዋል።


የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሥራ ዘመኑን ያጠናቀቀ ሲሆን በመጪው አመት አዲስ መንግስት ይመሰረታል።


የመንግስት ምስረታ በዓልም ሆነ ድግስ እንደማይኖር ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።


ንጋቱ ሙሉ

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page