top of page

በአትላንቲክ ውቅያኖስ የገባችበት የጠፋውን ቱሪስቶች መጓጓዥ ጠላቂ ጀልባ ለማግኘት ሰፊ ፍለጋ እየተካሄደ መሆኑ ተሰማ

  • Jun 20, 2023
  • 1 min read

ሰኔ 13፣2015


በአትላንቲክ ውቅያኖስ የገባችበት የጠፋውን ቱሪስቶች መጓጓዥ ጠላቂ ጀልባ ለማግኘት ሰፊ ፍለጋ እየተካሄደ መሆኑ ተሰማ፡፡


ጠላቂዋ ጀልባ ከትናንት በስቲያ አንስቶ ግንኙነቷ መቋረጡን CNN በድረ ገጹ ፅፏል፡፡


ጠላቂዋ ጀልባ ቱሪስቶችን እና ተመራማሪዎችን ታይታኒክ መርከብ ወደ ሰጠመችበት ስፍራ በማጓጓዝ የምትታወቅ ነች ተብሏል፡፡


ግዙፏ መርከብ ታይታኒክ የሰመጠችው ከ111 ዓመታት በፊት እንደሆነ ዘገባው አስታውሷል፡፡


ወደዚያው ቱሪስቶችን እና ተመራማሪዎችን የምታጓጉዘው ጠላቂ ጀልባ 5 ሰዎችን እንዳሳፈረች ነው የገባችበት የጠፋው፡፡


የቀራት የእስትንፋስ መደገፊያ /ኦክስጂን/ ከ4 ቀናት ያልበለጠ በመሆኑ ፍለጋው ከጊዜም ጋር እሽቅድምደፍም ውስጥ የተገባበት ነው ተብሏል፡፡


ባሕር ጠላቂ መርከቦች ፣ አውሮፕላኖች እና ሄሌኮፕተሮች የተሰለፉበት ታላቅ የነፍስ አድን ጥረት እየተደረገ መሆኑን የካናዳ እና የአሜሪካ የባህር ሀይል ሹሞች ተናግረዋል፡፡



የኔነህ ከበደ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

 
 
 

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page