top of page

በአርሲው ግጭት የ11 ሰዎች ህይወት ማለፉን ከዚህ ውስጥ 8ቱ የፀጥታ አካላት መሆናቸወን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡

  • Jul 7
  • 1 min read

ሰኔ 30/2018


በአርሲው ግጭት የ11 ሰዎች ህይወት ማለፉን ከዚህ ውስጥ 8ቱ የፀጥታ አካላት መሆናቸወን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡


በዚህ ግጭት 22 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል ያሉ ሲሆን ከ90 በመቶ በላይ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው መመለሳቸወን አስረድተዋል፡፡


ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ይህንን ያሉት የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሳላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እየሰጡ ባለበት ወቅት ነው።

ከሃይማኖት ግጭቶች ጋር በተያያዘ ለተነሳላቸው ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ በቅርቡ በአርሲ የነበረውን ግጭት አንስተዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአርሲው ግጭት ምርጫውን ለማደናቀፍ ጥረት ሲያደርጉ ነበር ያሏቸው ኃይሎች በአዲስ አበባ እና በምርጫ አከባቢ ከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ ሲደረግ ስለነበር ወደ አንድ መንደር ሄደው አርሲ ላይ ጥቃት ፈፅመዋል ብለዋል።


ምርጫውን ያደናቅፋሉ ያሏቸው ኃይሎች ለዚህ አላማቸው ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርጉ ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአዲስ አበባ የዕምነት ተቋማት ሳይቀር ቦምብ እና ክላሽ ስንለቅም ነበር ብለዋል።


የአርሲው ግጭት ምርጫውን የማደናቀፍ እንጂ የሃይማኖት መልክ የላቸውም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በቅርቡ በሰራነው ጥናት ከ50 በመቶ በላይ የእስልምና ዕምነት ተከታዮች ባለባቸው ወረዳዎች ከ1000 በላይ ቤተክርስቲያን ተገንብተዋል ብለዋል።


ታዲያ ግጭቱ ሃይማኖታዊ ቢሆን ኖሮ ከዚህ ሁሉ ወረዳዎች ለምን በጥቂት ወረዳዎች ውስጥ ብቻ ሆነ? ሲሉ ጠይቀዋል።


አዲስ አበባ ተቀምጠው ጫት እየቃሙ ያለምንም መረጃ ግጭት የሚያራግቡ አካለት ጥንቃቄ አንዲያደርጉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስጠንቅቀዋል፡፡

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page