top of page

ሐምሌ 30፣2016 - በተጠናቀቀው የትምህርት ዘመን ብቻ ከ4 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች በግጭት ምክንያት ሳይማሩ ቀርተዋል ሲል ኮሚሽኑ አስረድቷል

  • sheger1021fm
  • Aug 6, 2024
  • 1 min read

በሀገሪቱ የቀጠለው ግጭት እና አለመረጋጋት ለንጹሃ መሞት፣ መቁሰል ንብረት መውደም እና መፈናቀል ምክንያት ሆኖ ቀጥሏል ተብሏል፡፡


በተለይም ግጭት ባለባቸው በኦሮሚያ፣ አማራ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በታጣቂዎች በሚፈፀም ጥቃት እና መንግስት ያንን ለመከላከል አልያም ለፍትህ ለማቅረብ በሚደርገው እንቅስቃሴ ውስጥ ንፁሃን እየሞቱ እና እየተጎዱ መሆኑን መንግስታዊው የሰብአዊ መብቶች ተቆርቋሪው ኢሰመኮ ተናግሯል፡፡


በግጭቶች መካከል ከሚገደሉት፣ ከሚቆስሉት፣ ከሚፈናቀሉት እና ንብረታቸው ከወደመባቸው ሰዎች ባሻገር አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰ ነው ተብሏል፡፡


በተጠናቀቀው የትምህርት ዘመን ብቻ በትምህርት ገበታ ላይ ላይ መኖር ሲገባቸው ከ4 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች በግጭት ምክንያት ሳይማሩ ቀርተዋል ሲል ኮሚሽኑ አስረድቷል፡፡


በግጭቱ የወደሙ የጤና ተቋማት እና መሰረተ ልማቶች እንዲሁም ገበሬዎች መተዳደሪያቸው የሆነውን የእርሻ ስራ እንዳይሰሩ አድርጓል ብሏል፡፡


ያሬድ እንዳሻው



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page