top of page

ሰኔ 4፣ 2016 - በባህርዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ ቦታ ይዘው እየሰሩ ያሉ እና አዲስ ለመግባት በሂደት ላይ የሚገኙ ባለሃብቶች የፀጥታ ችግር ተጽዕኖ እያሳደረባቸው ነው ተባለ

  • sheger1021fm
  • Jun 11, 2024
  • 1 min read

በባህርዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ ቦታ ይዘው እየሰሩ ያሉ እና አዲስ ለመግባት በሂደት ላይ የሚገኙ ባለሃብቶች የፀጥታ ችግር ተጽዕኖ እያሳደረባቸው ነው ተባለ።


በኢንዱስትሪ ፓርኩ ገብቶ ስራ ለመጀመር የማምረቻ ማሽኖችን ሲያጓጉዝ የነበረ አንድ የህንድ ኩባንያ በዚሁ የፀጥታ ችግር ምክንያት በየአካባቢው መስተጓጎል እንደገጠመው ሠምተናል።


በፓርኩ ካሉ ስምንት የማምረቻ ሼዶች አምስቱ በባለሃብቶች መያዛቸውን በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የማርኬቲንግ፤ ፕሮሞሽን እና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ምክትል ስራ አስፈጻሚ አቶ ዘመን ጁነዲ ነግረውናል።



コメント


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page