top of page

በሌተናል ጄኔራል ሐምዳን ዳጋሎ የሚመራው ፈጥኖ ደራሽ ሀይል በካርቱም የሚገኘውን የሱዳን ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያን ተቆጣጠርኩት አለ

  • Jun 29, 2023
  • 1 min read

ሰኔ 20፣2015


በሌተናል ጄኔራል ሐምዳን ዳጋሎ የሚመራው ፈጥኖ ደራሽ ሀይል በካርቱም የሚገኘውን የሱዳን ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያን ተቆጣጠርኩት አለ፡፡


RSF የተሰኘው ፈጥኖ ደራሽ ሀይል በካርቱም የሚገኘውን የፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መያዙን አስመልክቶ መግለጫ እንዳወጣ ሜኸር ድረ ገፅ ፅፏል፡፡


ፈጥኖ ደራሹ ታጣቂዎቹ ጠቅላይ መምሪያውን መቆጣጠራቸውን የሚያስተማምኑ ፎቶ ግራፎችን እዩልኝ ማለቱም ታውቋል፡፡


RSF የፖሊስ ጠቅላይ መምሪያውን የተቆጣጠረው ካለፈው ቅዳሜ አንስቶ ሲካሄድ በነበረው ከባድ ውጊያ ነው ተብሏል፡፡


የፈጥኖ ደራሹ ሀይል የተቆጣጠረው የፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የበርካታ ጦር መሳሪያዎች እና ጥይቶች መገኛ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡


በሱዳን መንግስት ጦር እና በፈጥኖ ደራሹ ሀይል መካከል ውጊያው ከ11 ሳምንታት በላይ ሆኖታል፡፡



የኔነህ ከበደ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
የነሐሴ 9 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ኮንጎ የኮንጎ ኪንሻሣው የኢቦላ ወረርሽኝ አድማሱን እያሰፋ ነው ተባለ፡፡ ወረርሽኙ ወደ ተጨማሪ ግዛትም መዛመቱን የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከያ እና መቆጣጠሪያ /አፍሪካ CDC/ መረጃ ማሳየቱን አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡ በኮንጎ የኢቦላ ወረርሽኝ ያዳረሳቸው ግዛቶች ብዛት 6 ደርሷል፡፡ ኢቱሪ ወረርሽኙ ከፍተኛ ጫና ያሳደረ

 
 
 
የነሐሴ 8 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#የተባበሩት_አረብ_ኢሚሬትስ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ በሆርሙዝ ወሽመጥ በሁለት መርከቦቼ ላይ ጥቃት ሰንዝራለች ያለቻትን ኢራንን በብርቱ ኮነነቻት ተባለ፡፡ ኢራን በነዳጅ ጫኝ መርከቦቻችን ላይ ጥቃት ሰንዝራለች ሲል ከበድ ያለ ተቃውሞውን ያሰማው የኢሚሬትስ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እንደሆነ አልጀዚራ እና AFP ፅፈዋ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page