top of page

የካቲት 25፣2016 - በሀይማኖት ተቋማት እና በንጹሃን ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን እንደሚያወግዝ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ተናገረ

Updated: Mar 5, 2024

በሀይማኖት ተቋማት እና በንጹሃን ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አወገዘ፡፡

ችግሮች በንግግር እንዲፈቱም ጥሪ አቅርቧል፡፡


‘’ንጹሀን የፖለቲካ ማወራረጃ ሊሆኑ አይገባም’’ ያለው ጉባኤው ‘’ተገቢ የሆነ ጥበቃ እና ከለላ ሊደረግላቸው ይገባል’’ ሲልም ተናግሯል፡፡


አሁን ላይ በየእምነት ተቋማት እና በንጹሀን ላይ የሚደርሰውን ሞትና ጉዳት ‘’ኢ ፍትሃዊ ነው’’ ብሎታል፡፡


የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ፀሀፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ ‘’ሁሉም በየእራሱ መንገድ መሄዱ፣ በመደማመጥና በመነጋገር የሚያምኑ ጥቂቶች መሆናቸው፤ ግጭቶች ጎልተው እንዲታዩ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል ናቸው’’ ሲሉ ለሸገር ተናግረዋል፡፡


ማርታ በቀለ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page