top of page

ሰኔ 9 2017 - የጎንደር ዩኒቨርሲቲ 4 ቢልየን ብር ወጪ አድርጌባቸዋለሁ ያላቸው፤ 22 ፕሮጀክቶችን አስመረቀ።

  • sheger1021fm
  • Jun 16
  • 1 min read

ምረቃው የተደረገው የዩኒቨርሲቲው 70ኛ ዓመት ምስረታና 100ኛ ዓመት የማስተማሪያ ሆስፒታል የሆነበትን በዓል ምክንያት በማድረግ ነው።


የካንሰር ጨረር ህክምና ማዕከል፣ ንፁህ የመጠጥ ውሃ፣ የህክምና ኦክስጅን ማምረቻ ማዕከልን ጨምሮ ዩኒቨርሲቲው ሲገነባቸው የነበሩ ሌሎች 22 ፕሮጀክቶች ናቸው የተመረቁት።


ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገርና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በምረቃው ላይ ተገኝተዋል።


ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የጎንደር ዩኒቨርስቲ የማስተማርያ ሆስፒታል ከአካባቢው ሰዎችን ከማከም ባለፈም የህክምና ባለሙያዎች እንደ ሃገር እንዲፈሩ አድርጓል፣ ይህም ስራ በተሻለ መንገድ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።


ዩኒቨርሲቲዎች እውቀትን ሲያስተላልፉ ያሉበትን ማህበረሰብ ማዕከል ማድረግ አለባቸው፣ ጎንደር የዕውቀት ማዕከል ናት ፣ነባር ዩኒቨርስቲው ነባሩን እውቀት በተሻለ መንገድ እንዲሰፋ ማድረግ ያስፈልጋል  ሲሉ ጠቅሰዋል።


ዩኒቨርስቲው ዋንኛ አላማው ሊሆን የሚገባው ተወዳዳሪና ጥራት ያለው የሰው ሃይል በዕውቀት መፍጠር ላይ ሊበረታ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

ree

የጎንደር ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት አስራት አፀደወይን(ዶ/ር) ኡሁን የተመረቁ ፕሮጀክቶች ዩንቨርስቲው ራስ ገዝ ለመሆን በሚያደርገው ስራ አጋዥ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።


ከዚህ ቀደም በጎንደርና በአካባቢው የካንስር ታካሚዎች የጨረር ህክምና ለማግኘት ወደ አዲስ አበባ ፣ ጅማ እና ሀዋሳ ለመሄድ ይገደዱ ነበር ተብሏል።


አሀን የተመረቀው የካንሰር ጨረር ህክምና ማዕከል እንደ ሃገር 5ተኛ ማዕከል ሲሆን በአማራ ክልል ደግሞ ብቸኛ መሆኑን ሰምተናል።


የጎንደር ዩኒቨርስቲ ጎንደር ከተማ ከሚያቀርበው የውሃ አቅርቦት ወደ 20 ከመቶ ይወስድ ነበር የተባለ ሲሆን የተመረቀው የውሃ ፕሮጀክት ዩኒቨርስቲው የውሃ ፍላጎቱን በራሱ አቅም እንዲችል ያደርገዋል ተብሏል።


የፍሳሽ ቆሻሻን በተገቢው መንገድ አክሞ  ለአትክልት ውሃ ማጠጣትና ለሌሎች አገልግሎቶች እያዋለ ሲሆን ለንፁህ የመጠጥ ውሃ ለመጠቀም ዩንቨርስቲው ማቀዱን ተናግሯል።


ከተመረቁት ፕሮጀክቶች ውስጥ 17 የሚሆኑት አዲስ የተገነቡ ሲሆን ቀሪዎቹ ነባር መሆናቸውን ሰምተናል።


ሃያዎቹ ፕሮጀክቶች በመንግስት በጀት 2ቱ ደግሞ በአጋር አካላት ድጋፍ የተገነቡ ናቸው።


በረከት አካሉ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page