top of page

ሰኔ 6፣ 2016 - ከዓለም አጠቃላይ ህዝብ 1 ቢሊዮን የሚያህለው በተለያዩ የአእምሮ ህመም ተጠቂ ሆኗል፡፡

  • sheger1021fm
  • Jun 13, 2024
  • 1 min read

ከዓለም አጠቃላይ ህዝብ 1 ቢሊዮን የሚያህለው በተለያዩ የአእምሮ ህመም ተጠቂ ሆኗል፡፡


እንደ ኢትዮጵያ ያሉ አነስተኛ  ገቢ ያላቸው ሀገራት ዜጎች ደግሞ የበለጠ  ተጠቂ ሆነዋል፡፡


ይኽንን የተናገሩት፣ በአዕምሮ ህመም ላይ በርካታ ጥናቶችን ያደረጉት ኘ/ር አታላይ ዓለም፤ የአማኑኤል ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተሀድሶ ህክምናን በተመለከተ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ነው።



1 ቢሊዮን የሚያህለው የአለም ሕዝብ፤ በቁጥር 300 በሚሆኑ የአዕምሮ ሕመም ችግሮች ውስጥ እንደሚገኝ በጥናት መረጋገጡ ተጠቅሷል፡፡


በኢትዮጵያ ይህንን የአእምሮ ህመም የሚያደርሰው ማህበራዊ ቀውስን ለመቀነስ ''የተሀድሶ ህክምና'' ላይ መስራት ቢያስፈልግም ግን ስለ ተሀድሶ ህክምና በኢትዮጵያ ያለው ግንዛቤም ደካማ መሆኑን ፕሮፌሰር አታላይ ተናግረዋል፡፡ 


የአእምሮ ህመም  ያለባቸው ሰዎች፣ ከሌላው ሰው በአማካኝ ከ10 እስከ 20 ዓመት ቀድመው የመሞት እድል እንዳላቸውና ራሳቸውን ከሚያጠፉ 10 ሰዎች መካከል በአማካይ 9ኙ የአዕምሮ ህመም ያለባቸው ሆነው እንደሚገኙ ጥናቱ ማሳየቱ ተነግሯል።


ማንያዘዋል ጌታሁን


Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page