top of page

ሰኔ 6፣ 2016 - ኢትዮጵያ የግብርና ምርቶችን በግብአትነት ለሚጠቀሙ ኢንዱስትሪዎች ትኩረት ብትሰጥ ያላትን ተወዳዳሪነትም እንደምታሻሽል ባለሞያ ተናገሩ

  • sheger1021fm
  • Jun 13, 2024
  • 1 min read

ኢትዮጵያ የግብርና ምርቶችን በግብአትነት ለሚጠቀሙ ኢንዱስትሪዎች ትኩረት ብትሰጥ በአለም ገበያ ያላትን ተወዳዳሪነትም እንደምታሻሽል ባለሞያ ተናገሩ።


የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የተመሰረተው ግብርና ላይ በመሆኑ ኢንዱስትሪዎች በዚሁ ላይ ቢያተኩሩ የተሻለ ነው ተብሎዋል፡፡


80 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ አርሶ አደር በመሆኑ ጠቀሜታው የጎላ ነው የተባለ ሲሆን፤ ለኢንዱስትሪው ትልቁን ግብአት የሚያቀርበው ግብርናው እንደሆነም ባለሞያው ተናግረዋል፡፡


ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ግብርና መር ኢንዱስትሪን እንደምትከተል እና አሁን ላይ ግን ሁሉንም አካታች ዘርፍ እንደምትከተል ሰምተናል፡፡


በሀገር ውስጥ በቂ የሆነ የግብርና ምርት ካለ ከውጭ ጥሬ ዕቃ አምጥቶ ማምረት አዋጭ እንዳልሆነ ባለሞያው ለሸገር ተናግረዋል፡፡




Commenti


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page