top of page

ሰኔ 5፣ 2016 - ተሻሽሎ የተሰናዳው የመንግስት ሰራተኞች ረቀቅ አዋጅ 2 ጊዜ የብቃት ምዘና ወስደው መካከለኛ ውጤት ያመጡ ከስራ እንዲሰናበቱ ይደነግጋል

  • sheger1021fm
  • Jun 12, 2024
  • 1 min read

ተሻሽሎ የተሰናዳው የፌዴራል የመንግስት ሰራተኞች ረቀቅ አዋጅ ሁለት ጊዜ የብቃት ምዘና ወስደው ዝቅተኛ ውጤት ያመጡ ከስራ እንዲሰናበቱ ይደነግጋል፡፡


ይሁንና ምዘናው ገለልተኝነቱ የተጠበቀ ነው ወይ? የሚል ጥያቄ ይነሳበታል፡፡


ረቂቅ አዋጁ የብቃት ምዘናን ጨምሮ የተለያዩ የማሻሻያ ድንጋጌዎች እንዲታከሉበት ተጠይቋል፡፡


በረቂቅ ሕጉ ላይ ዛሬ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ውይይት ተካሄዷል፡፡


በህጉ ሊካተቱ እና ግልፅ ሊሆኑ ይገባል ተብለው ከተነሱ ነጥቦች መካከል


• የመንግስት ሰራተኛው ለቤት ኪራይ እና ለትራንስፖርት ተብሎ የሚሰጣቸው ጥቅማ ጥቅም ላይ ዳግም ታክስ መክፈል የለባቸውም፡፡


• የሰራተኞች ምዘና በትውውቅ እና በብሔር መጠቃቀሚያ እንዳይሆን ነፃ እና ገለልተኛ ሆኖ ስለሚካሄዱ የሚረጋገጥበት ዘዴ መኖር አበለት፡፡


• ሲቪል ሰርቪሱ ብሔር ብሔረሰቦችን ይምሰል ሲባል ምን ማለት እንደሆነ የኮሚሽኑ አቋም ምንድነው?


• እንደ ገቢዎች ሚኒስቴር እና ጉምሩክ ኮሚሽን ላሉ ተቋማት ህጉ ከፊል ነፃነት ሊሰጣቸው ይገባል፡፡



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page