top of page

ሰኔ 4፣ 2016 - የዋጋ ንረቱ በመጪው ዓመትም ባለሁት አሃዝ ሆኖ እንደሚቀጥል ተተነበየ

  • sheger1021fm
  • Jun 11, 2024
  • 1 min read

የዋጋ ንረቱ በመጪው ዓመትም ባለሁት አሃዝ ሆኖ እንደሚቀጥል ተተነበየ፡፡


በመጪው ዓመት አጠቃላይ የዋጋ ንረቱ 12 በመቶ እንደሚሆን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል፡፡


የፍጆታ እቃዎች እና የአገልግሎት የዋጋ እድገት፤ እየተገባደደ ባለው የበጀት ዓመት የመቀነስ አዝማሚያ እያሳየ ቢሆንም ባለሁለት አሃዝ ሆኖ እንደሚቀጥል መገመቱን ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ተናግረዋል፡፡

ግሽበቱ በግንቦት ወር መጨረሻ ከነበረበት 27.4 በመቶ በመጭው ዓመት ወደ 12 በመቶ ዝቅ እንዲል ለማስቻልም ጥብቅ የገንዘብ እና ፊሲካል ፖሊሲ እርምጃዎች ይወሰዳሉ ብለዋል ሚኒስትሩ፡፡


የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ የ2017 አመትን የመንግስት ረቂቅ በጀት ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ሲያቀርቡ ነው ይሄንን ያሉት፡፡

Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page