top of page

ሰኔ 28 2017 - ሂጅራ ባንክ በዘንድሮው የሂሳብ ዓመት ከ840 ሚሊዮን ብር በላይ ትርፍ አገኘሁ አለ።

  • sheger1021fm
  • 4 days ago
  • 1 min read

ሂጅራ ባንክ በዘንድሮው የሂሳብ ዓመት ከ840 ሚሊዮን ብር በላይ ትርፍ አገኘሁ አለ።


ይህም ውጤት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ740 በመቶ ጭማሪ አለው ሲል አስረድቷል።


ባንኩ በበጀት ዓመቱ ከ1.8 ቢሊዮን ብር በላይ ጠቅላላ ገቢ መሰብሰቡንም ጠቅሷል።


ይህም ባንኩ ባለፈው ዓመት ካስመዘገበው ጠቅላላ ገቢ 148.85 በመቶ እድገት አሳይቷል ሲል ለሸገር በላከው መግለጫ ጠቅሷል።

የባንኩ ጠቅላላ ሀብት ከ15 ቢሊዮን ብር አልፏል፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 95.37 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል ተብሏል።


እንዲሁም የተቀማጭ ገንዘብ መጠን 12 ቢሊዮን ብር መድረሱም ተጠቅሷል።


በተጨማሪም ሂጅራ ባንክ በበጀት ዓመቱ 40 ሚሊዮን ዶላር አግኝቻለሁ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 304.5 በመቶ ጭማሪ ያሳያል ብሏል።


135 ቅርንጫፎች፣ የደንበኞችን ብዛት ደግሞ 931,148 ደርሰዋል ሲል ጠቅሷል።


ሂጅራ ባንክ የኦምኒ ፕላስ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ተጠቃሚዎች ከ350,000 በላይ ሲሆኑ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 141.86 በመቶ እድገት ያሳያል ተብሏል።


ባለፉት 6 ወራት ብቻ የሀላል ፔይ ዋሌት ተጠቃሚዎች ከ811,000 በላይ ደርሰዋል የተባለ ሲሆን  ያለማስያዣ የፋይናንስ አገልግሎት መጠቀም የሚያስችል ኢ-ሙራባሃ የፋይናንስ አገልግሎትን በዋሌት በማስጀመር ስኬታማ ዓመትን አሳልፌያለሁ ብሏል።


ንጋቱ ሙሉ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page