top of page

ሰኔ 27፣ 2016 - ‘’የሰብአዊ መብት የሚባል አዋጅ፣ ተቋማት እና አሰራርን፤ መፈተሸ የስፈልጋል’’ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ

  • Jul 4, 2024
  • 1 min read

‘’የሰብአዊ መብት የሚባል አዋጅ፣ ተቋማት እና አሰራርን፤ መፈተሸ የስፈልጋል’’ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡


ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአንድ የፓርላማ አባል በሀገሪቱ የሰብአዊ መብት ጥሰት፣ የጅምላ ግድያዎች እስራቶች በመንግስት ሀይሎች እየተፈጸመ ነዉ የሚል ጥያቄ በቀረበላቸዉ ወቅት ነው ይህንን የተናገሩት፡፡


የሰብአዊ መብት በግርድፉ ሲታይ ‘’ደስ የሚል ቋንቀ ነዉ’’ ያሉት ዐቢይ አህመድ ‘’የሰብአዊ መብት የሚባል አዋጅ፣ ተቋማት እና አሰራርን መፈተሸ የስፈልጋል እኛ ደመወዝ የማንከፍለዉ፣ ሌሎች ሃይሎች የቀጠሩት፣ ለሌሎች ሪፖርት የሚያደርግ ተቋም ኢትዮጵያ ዉስጥ ከፈቀድን ምን ሊፈጠር እንደሚችል ለእናንተ መተዉ ነዉ’’ ሲሉ ለእንደራሴዎቹ ነግረዋል፡፡


‘’በየትም ቦታ ያሉ እኔ የማያቸዉ የሰብአዊ መብት ተቋማት ልክ እንደ መርፌ የራሳቸዉን ቀዳዳ መስፋት የማይችሉ እና የራሳቸዉን ድክመት ማየት የማይችሉ ናቸዉ’’ ብለዋል፡፡


‘’ይሄ ጥሩ አይደለም ሀገር ያፈርሳል ተቋሞቻችን ፅዱ ማድረግ አለብን፤ እነዚህ ተቋማት ከሁለት ተጽእኖ ነጻ መዉጣት አለባቸዉ’’ ብለዋል፡፡


‘’ከኢትጵያ መንግስት ተጽኖ ነጻ መሆን አለባቸዉ፤ ከሌላም ሀገራት ተጽእኖዎች ነጻ መሆን አለባቸዉ፤ አሁን ያሉት ከኛ ነጻ ሆኑና እንደዚያ አይሰራም’’ ሲሉ ተናግረዋል፡፡


ያሬድ እንዳሻው


Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page