top of page

ሰኔ 26፣ 2016 - ምጣኔ ሐብት - የአፍሪካ ሀገሮች ብድር ከፍተኛ ነው ተባለ

የአፍሪካ ሀገሮች ብድር በጠቅላላው 2 ትሪሊየን ዶላር መድረሱ ተሰምቷል።


ይህም ሀገሮቹ አጠቃላይ ካላቸው ሀብት ወይም ብሔራዊ ምርት 65 በመቶ ነው።


ይህ ብድር በጠቅላላው ብሔራዊ ምርት 50 በመቶ መብለጥ እንደሌለበት ጥናት ተናግሯል።


የብዙዎቹ ሀገሮች ብድር ከመክፈል አቅማቸው በላይ ነው ።


ለአፍሪካ ልማት ባንክ በቀረበው ጥናት መሰረት አብዛኛዎቹና ትልቅ ተበዳሪዎች ሀገሮች ከ4 አይበልጡም።

ትልቋ ተበዳሪ ሀገር ደቡብ አፍሪካ ስትሆን 288 ቢሊየን ዶላር ተበድራለች


ናይጄሪያ 181 ቢሊየን ዶላር፣ አልጄሪያ 102 ቢሊየን ዶላር፣ ሞሮኮ 92 ቢሊየን ዶላር የተበደሩ ናቸው።


እነዚህ ሀገሮች የአፍሪካን ብድር 60 በመቶ ወስደዋል።


የተቀሩት የአፍሪካ ሀገሮች 745 ቢሊየን ዶላር ብድር ወስደዋል።


ተህቦ ንጉሴ


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page