top of page

ሰኔ 26፣ 2016 - ሀገርን ከፍተኛ አደጋ ላይ የሚጥለውን የኬሚካል ክምችት ለማስወገድ ምን እየተሰራ ይሆን?

  • sheger1021fm
  • Jul 3, 2024
  • 1 min read

በህንጻ ግንባታ ላይ የደህንነት መከላከያ ባላሟሉ አስገንቢዎች ላይ እስከ እስራት የሚያደርስ ህግ መዘጋጀቱ ተሰማ።


አዲሱ ህግ ስራ ላይ ሲውል በህንጻ ግንባታ ላይ የሚስተዋሉ የደህንነት ችግሮች እና ስጋቶችን ይቀርፋልም ተብሎለታል።


በህንጻ ግንባታ ላይ በሚስተዋሉ የጥንቃቄ ጉድለት፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሰዎች ሞት እና የአካል ጉዳት እየጨመረ መምጣቱ አዲሱ ህግ እንዲወጣ ምክንያት ሆኗልም ተብሏል።


በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የኮንስትራክሽንና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ መዲና አህመድ፤ ህንፃዎች በሚገነቡበት ሰዓት በአካባቢው እና በህብረተሰቡ ላይ ስጋት በሆነ መልኩ በሚገነቡና ለሰራተኞቻቸው ጭምር የደህንነት መከላከያ ግብአቶች ሳያሟሉ በተገኙ አስገንቢዎች ላይ ከፈቃድ መቀማት እስከ እስራት ድረስ እንዲቀጡ በህጉ ተቀምጧል ሲሉ ነግረውናል።


ከዚህ ባለፈም የስራ ተቋራጮች የብቃት ማረጋገጫ ከሌላቸው ወደ ስራ እንዳይገቡም ህጉ ይከለክላል ብለዋል።


አዲሱ ህግ በሰራተኞች እና በአካባቢው ባሉ ማህበረሰቦች ላይ በጥንቃቄ ጉድለት ምክንያት ጉዳት እንዳይደርስ የቅድመ መከላከል ስራ እንዲሰራ እና ጥንቃቄ እንዲደረግ በማሰብ እንጂ በህንፃ አስገንቢዎች ላይ ጫና ለማሳደር አይደለም ሲሉ ወ/ሮ መዲና ተናግረዋል።


ህጉ መቼ እንደሚፀድቅ እና የእስር ቅጣቱ እስከ ምን ያህል ጊዜ የሚለውን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጎበት ሲፀድቅ ይፋ እንደሚደረግም ስራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል።


ፍቅሩ አምባቸው


Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page