top of page

ሰኔ 25፣ 2016 - ደንበኞች አገልግሎት ለማግኘት ወደ ባንክ ቅርንጫፎች መሄድን የሚያስቀረው ቨርችዋል ባንኪንግን የሚጠቀመው ተገልጋይ ቁጥር እየጨመረ ነው ተባለ

ደንበኞች አገልግሎት ለማግኘት ወደ ባንክ ቅርንጫፎች መሄድን የሚያስቀረው ቨርችዋል ባንኪንግን የሚጠቀመው ተገልጋይ ቁጥር እየጨመረ ነው ተባለ፡፡


የባንኮችን ቅርንጫፍ ከመጨመር ይልቅ ቨርችዋል ባንኪንግ አገልግሎት የሚሰጡትን ማስፋት የተሸለ እንደሆነ አቢሲኒያ ባንክ ይናገራል፡፡


ባንኮች የሚከፍቱትን ቅርንጫፎች አብዝቶ 24 ሰዓት ማሰራቱ በተለያዩ ምክንያቶች ዘርፉን ውጤታማ አያደርገውም ያሉት በአቢሲኒያ ባንክ የዲጂታል ባንኪንግ ኦፕሬሽን ክፍል ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ረታ የቨርችዋል ባንኪንግ ቴክኖሎጂው ግን አገልግሎቱን የተሸለ ያደርግልናል ብለዋል፡፡


ቴክኖሎጂው ለኢትዮጵያውያን ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ደግሞ የተጠቃሚውም ቁጥር እንዲጨምር አድርጎታል የሚሉት አቶ ዳንኤል በዚህም አቢሲኒያ ባንክ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች 35 ማእከላት ለደንበኞች አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሆኑ ተናረዋል፡፡


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page