top of page

ሰኔ 24 2017 -''ጨረታ ወጥቶላቸው የግንባታ ስራቸው የተጀመሩ መንገዶችን ብቻ ለመጨረስ 500 እስከ 600 ቢሊየን ብር ያስፈልጋል ''

  • sheger1021fm
  • Jul 1
  • 1 min read

ከዚህ ቀደም የተጀመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች ቢኖሩም በወቅቱ ባለመጠናቀቃቸው ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል ተባለ፡፡


መንግስት ለመንገድ ፕሮጀክቶች የሚደለድለው በጀት ይበል የሚያሰኝ ቢሆንም አንዳንድ አካባቢዎች ላይ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች የበለጠ ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባ ተነስቷል፡፡


ይህ ጥያቄ የተነሳው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ2018 ረቂቅ በጀት ላይ በሚያደርገው ውይይት ላይ ነው፡፡


ሁለት ክልሎችን ያገናኛል የተባለው የነቀምት ቡሬ መንገድ ግንባታ እስካሁን ያልተጠናቀቀ መሆኑን ያነሱት የምክር ቤት አባሉ አቶ ብዙአየሁ ደገፋ ሌላኛው ጋምቤላን እና ደንቢዶሎን የሚያገናኘው የመንገድ ግንባታም ስራው አለመጀመሩን አንስተዋል፡፡

በሌላ በኩል እቅድ የተያዘላቸው የመንገድ ፕሮጀክቶች በ2018 በጀት ዓመት ውስጥ ያልተካተቱ መኖራቸውን ያነሱት የምክር ቤት አባሉ ለእነሱ ወደፊት ምን እንደታሰበ ጠይቀዋል፡፡


የ2018 ረቂቅ በጀት ላይ ከምክር ቤት አባላቱ ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ የምክር ቤቱ አባላት የተነሱት ጥያቄዎች ተገቢ ናቸው ብለዋል፡፡


ምክር ቤቱ ያፀደቃቸውን የመንገድ ፕሮጀክቶች ለመጨረስ 1.5 ትሪሊየን ብር ያስፈልጋል ያሉት ሚኒስትሩ ጨረታ ወጥቶላቸው የግንባታ ስራቸው የተጀመሩ መንገዶችን ብቻ ለመጨረስ 500 እስከ 600 ቢሊየን ብር ያስፈልጋል ብለዋል፡፡


ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





 
 
 

Commenti


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page