top of page

ሰኔ 24፣ 2016 - እውን እንደተባለው ዲጂታል እና ስማርት ከተማ እየሆነች ነው ወይ

በአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞች የነበሩት ሰበታ፣ ቡራዩ፣ ለገጣፎ ለገዳዲ፣ ሱሉልታ፣ ገላንና መናገሻ፤እንዲሁም 40 የገጠር ቀበሌዎች ባለፈው ዓመት ጥር ወር “የሸገር ከተማ አስተዳደር’’ በሚል በአንድ መደራጀታቸው ይታወሳል።


የከተማ አስተዳደሩ በስሩ 12 ክፍለ ከተሞች እና 36 ወረዳዎችን ይዞ ነው የተደራጀው።


የሸገር ከተማ አስተዳደርን በአዲስ መልክ ማደራጀት ያስፈለገው በዋናነት ለነዋሪዎቹ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እንደሆነ ተጠቅሷል።


ለዚህም ሲባል ከተማዋን ‘’ስማርት እና ዲጂታል’’ የማድረግ ስራ ይሰራል ተብሏል።


ለመሆኑ የከተማ አስተዳደሩ በአዲስ መልክ ከተደራጀ በኋላ ባሉት አንድ ዓመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ምን ተሰርቷል?


እውን እንደተባለው ዲጂታል እና ስማርት ከተማ እየሆነች ነው ወይ ስንል ጠይቀናል?


ንጋቱ ረጋሳ



Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page