top of page

ሰኔ 24፣ 2016 - ኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ4 ቢሊየን ዶላር በላይ እያወጣች ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ ታስገባለች

  • sheger1021fm
  • Jul 1, 2024
  • 1 min read

ኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ4 ቢሊየን ዶላር በላይ እያወጣች ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ ታስገባለች፡፡


ነገር ግን በየጊዜው በመሀል ሀገር ስራና ቢዝነስ ባለበት ከተማ ነዳጅ ይጠፋል።


ግዜ እየጠበቀ በየማደያ ቸርቻሪዎች ጋር የሚታየው እረጃጅም ሰልፍና መንፏቀቅ ከየት የመጣ ነው?


ነዳጅ ገብቷል፤ ተገዝቷል ከተባለስ ለምን ሰልፍና የማደያ ላይ ትርምስ ጠባይ እየሆነ መጣ?


በዓመት ቢያንስ ከሶስት ግዜ በላይ ይህ ነገር በየማደያ አዳዮች ይታያል፡፡


በዚህ ጉዳይ የጠየቅናቸው የኢትዮዽያ ነዳጅ አዳዮች ማህበር ዋና ፀሐፊ አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ ችግሩ መፈተሽ አለበት ይላሉ።


ስራና ቢዝነስ በሚበዛበት ቦታም የሚሰጠው የነዳጅ ኮታና ስርጭት ችግር መፍጠሩን አስረድተዋል፡፡


የኢትዮዽያ የነዳጅ አቅራቢዎች ድርጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ እስመለአለም ምህረቱ የሚታየው ችግር ከ ኮንትረኦባንድ ጋር የተገናኘ አይደለም እጥረትም የለም ይላሉ፡፡


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page