top of page

ሰኔ 21፣ 2016 - ዘርፉ በክልሉ ያላደገበት ምክንያት ምን እንደሆነ ጠይቀናል

  • sheger1021fm
  • Jun 28, 2024
  • 1 min read

አጠቃላይ ካፒታላቸው ከስድስት መቶ ሺህ እስከ አስር ሚሊየን ብር የሆኑ እና ከስድስት እስከ ሃምሳ የሚሆኑ ሰዎችን፤ በስራቸው ይዘው የሚያሰሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች አነስተኛ በሚል ይጠራሉ።


ካፒታላቸው ከአስር ሚሊየን እስከ ዘጠና ሚሊየን ብር የሆኑት እና ከሃምሳ አንድ እስከ መቶ ሰዎችን፤ ይዘው የሚያሰሩት ደግሞ መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች በሚል ይታወቃሉ።


እንደዚህ አይነት 25,200 አነስተኛ እና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች በአገር አቀፍ ደረጃ እንዳሉ ሠምተናል።


የእነዚህ ኢንዱስትሪዎች ስርጭት በክልሎች የተመጣጠነ እንዳልሆነ ግን የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት፤ የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ አሸናፊ መለሠ ተናግረዋል።


ለአብነትም በአፋር ክልል ስለሚገኙ አነስተኛ እና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች ብዛት ከአንድ መቶ አይበልጡም ብለዋል።


ዘርፉ በክልሉ ስላላደገበት ምክንያት ምን እንደሆነ ጠይቀናል፡፡



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page