top of page

ሰኔ 19፣ 2016 - ለመንግስት ሆስፒታሎች ከሚቀርቡና በብዙ የውጭ ምንዛሬ የሚሸመቱ የመመርመሪያ መሳሪያዎች ተገቢውን አገልግሎት ሳይሰጡ ከስራ ውጭ ሲሆኑ ይታያል

ለመንግስት ሆስፒታሎች ከሚቀርቡና በብዙ የውጭ ምንዛሬ የሚሸመቱ የመመርመሪያ መሳሪያዎች ተገቢውን አገልግሎት ሳይሰጡ ከስራ ውጭ ሲሆኑ ይታያል፡፡


ይህም መሳሪያዎቹ በቂ መለዋወጫ እንዲሁም ለስራው የሚያስፈልጉ ኬሚካሎች ያልተሟሉላቸው በመሆኑ ነው ሲሉ የጤና ተቋማቱ ይናገራሉ፡፡


ለመንግስት የጤና ተቋማት የህክምና መሳሪያዎችን የሚያቀርበው የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በበኩሉ በዚህ ላይ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት ግብዓቶቹን ከሚያቀርቡ ድርጅቶች ጋር ለ3 ዓመታት ሳይቆራረጥ እንዲቀርብ ውል እያሰርኩ ነው ብሏል፡፡


በህክምና ግብዓት አቅርቦቱ ላይ የሪኤጀንቶች ስርጭት ያልተቆራረጠ እንዲሆን የመንግስትና የግል አጋርነት ወይም ፐብሊክ ፕራይቬት ፓርትነርሽፕ አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ መታሰቡን የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ም/ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ንጉሴ ተናግረዋል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ ይህንን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ…


ምህረት ስዩም


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page