top of page

ሰኔ 18፣ 2016 - በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ከተሰማሩት በአለም አቀፍ ደረጃ የተከለከሉ ፀረ ተባይ መድኃኒቶችን የሚጠቀሙ እንዳሉ ተነግሯል

  • Jun 25, 2024
  • 1 min read

ኢትዮጵያ ውስጥ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ከተሰማሩት በአለም አቀፍ ደረጃ የተከለከሉ ፀረ ተባይ መድኃኒቶችን የሚጠቀሙ እንዳሉ ተነግሯል።


በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የባዮሎጂ እና አካባቢ ብክለት ምርምር ትምህርት ክፍል በቅርቡ ባደረገው ጥናት ይህንኑ አረጋግጫለሁ ብሏል።


እንደ ዝዋይ፤ ሃዋሣ እና አርባ ምንጭ ያሉ አካባቢዎችን በሚያካልለው ‘’የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ’’እየለሙ ባሉ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶቹ ላይ የተካሄደው ይኸው ጥናት ፀረ ተባይ መድሃኒቶቹ እና ኬሚካሎቹ በኮንትሮባንድ እንደሚገቡ ያመለክታል።


የጥናት ቡድኑ መሪ ዶክተር ዳንኤል ወ/ሚካኤል በአለም አቀፍ ደረጃ ሲከለከሉ እንዲወገዱ ባለመደረጋቸው አሁም ድረስ ከክምችት እየወጡ ጥቅም ላይ እየዋሉ ነው ብለዋል።



Recent Posts

See All
በ'ፊንቴክ' የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ፖሊስ የጠየቀው የተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ ላይ ለመወሰን ፍርድ ቤት ለነገ ቀጥሯል።

ከ"ፊንቴክ" (Fintech) ኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘ በከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ዛሬ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። መርማሪ ፖሊስ በቀሪ የምርመራ ስራዎች ምክንያት ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page