top of page

ሰኔ 17 2017 - የ7 ዓመት ታዳጊ በመኖሪያ ጊቢ ውስጥ ባለ የፍሳሽ ማጠራቀሚያ ታንከር ውስጥ ወድቆ ሕይወቱ አለፈ

  • sheger1021fm
  • Jun 24
  • 1 min read

ትናንት ከሰዓት በኋላ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የ7 ዓመት ታዳጊ በመኖሪያ ጊቢ ውስጥ ባለ የፍሳሽ ማጠራቀሚያ ታንከር ውስጥ ወድቆ ሕይወቱ አለፈ፡፡


ከአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን እንደሰማነው በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ተከማ ወረዳ 14 ጋርመንት አካባቢ ነው ታዳጊው በመኖሪያ ጊቢ በነበረ የውሃ ማጠራቀሚያ ታንከር ውስጥ ወድቆ የሞተው፡፡


የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሞያው አቶ ንጋቱ ማሞ እንደነገሩን በመኖሪያ ጊቢ የሚገኙ የፍሳሽ ማጠራቀሚያዎች ክዳን ካልተበጀላቸው አደጋው የከፋ ስለሚሆን ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል፡፡


ከዚህ በፊትም በቂርቆስ ክፍለ ከተማ መስቀል ፍላወር አካባቢ በመኖሪያ አፓርታማ ቅጥር ግቢ እንደዚሁም በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አዲሱ ሚካኤል አካባቢ ባለ ኮንዶሚኒየም ጊቢ ውስጥ ክዳንና መከላከያ ባልተደረገላቸው የፍሳሽ ማጠራቀሚዎች ውስጥ ሁለት ታዳጊዎች ወድቀው ህይወታቸው አልፏል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page