top of page

ሰኔ 14፣ 2016 - አንዳንድ የውጭ ባለሃብቶች በተሳሳተ መረጃ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ለቀው እየሄዱ ነው ተብሏል

  • sheger1021fm
  • Jun 21, 2024
  • 1 min read

አንዳንድ የውጭ ባለሃብቶች በተሳሳተ መረጃ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ለቀው እየሄዱ ነው ሲል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ተናገረ።


በዚህም ምክንያት ሁሉንም ችግር ተጋፍጠው የሚሰሩ የሀገር ውስጥ ባለሃብቶችን ለመሳብ እና በሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ በሀገር ውስጥ ባለሃብቶች እንዲሸፈን የተለያዩ የአሠራር ማሻሻያዎች መደረጋቸውም ተነግሯል።


የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አክሊሉ ታደሰ በሀገሪቱ አንዳንድ ችግሮች ሲከሰቱ የውጭ ባለሀብቶች በትዕግስት ነገሮችን ከማየት እና ትክክለኛውን መረጃ ከማጣራት ይልቅ በተሳሳተ መረጃ ከዘርፉ በቶሎ ይወጣሉ ብለዋል።


የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ግን ችግሮች ቢከሰቱም ስራቸውን በፅናት ስለሚቀጥሉ ለሀገር ውስጥ ባለሃብት ትኩረት እንድናደርግ ምክንያት ከሆኑን ውስጥ አንዱ ነው ሲሉ ነግረውናል።


የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችን ወደ ኢንቨስትመንት ገብተው መዋዕለ ነዋያቸውን ፈሰስ እንዲያደርጉ ለማበረታታት የተለያዩ የአሰራር ማሻሻያዎችን አድርገናል የሚሉት ዋና ስራ አስፈጻሚው ከተደረጉ ማሻሻያዎች የታሪፍ ማሻሻያ እና የመሬት ኪራይ ክፍያ አንዱ ነው ብለዋል።


ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ አክሊሉ ታደሰ አክለውም የሀገር ውስጥ አምራቾችን ለማበረታታትም በአገር ውስጥ የሚመረት ምርት ከውጪ እንዳይገባና ከሀገር ውስጥ አምራቾች እንዲገዛ መወሰኑንም ተናግረዋል።


በኢትዮጵያ አሁን ላይ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ከሚገኙ ኢንቨስተሮች ውስጥ 55 በመቶው የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች መሆናቸውንም ሰምተናል።



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page