top of page

ሰኔ 13፣ 2016 - የዲጂታል መታወቂያ የያዘ ሰው ቁጥር 1.7 ሚልየን እንደደረሰ ሰምተናል

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በሙሉ ከ2 ሳምንት በኋላ ዲጂታል መታወቂያ በእጃቸው ሊኖር ይገባል ተብሏል፡፡


የቀድሞዉን የወረቀት መታወቂያ በዲጂታል በመቀየሩ ስራ፤ ከ2 ሚልየን በላይ ነዋሪዎች ተጠቃሚ እንደሆኑ ተነግሯል፡፡


ቀሪዎቹ በሁለት ሳምንት ውስጥ መታወቂያቸውን ዲጂታል እንዲያደርጉት ይጠበቃልም ተብሏል፡፡


ይህንን ያለው የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል መዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ነው፡፡


ከዚህ ቀደም አሻራ ያልሰጡ ከ5 መቶ ሺህ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎች፤ ለዲጂታል መታወቂያ በአዲስ መልክ እንደተመዘገቡም ተነግሯል፡፡


የዲጂታል መታወቂያ የያዘ ሰው ቁጥር 1.7 ሚልየን እንደደረሰ ሰምተናል፡፡


ይህ የሚያሳየው ደግሞ የወረቁትን መታወቂያ የምይዘው ሰው ቁጥር በእጅጉ መቀነሱን ነው ሲል ኤጀንሲው አስረድቷል፡፡


አዲስ መታወቂያ የሚያወጡ ሰዎች የወረቁቱን መታወቂያ እንደማይሰጣቸው ተነግሯል፡፡


ታመው በአልጋ ላይ ያሉ፣ በእድሜ የገፉ ሰዎች እና በተለያዩ ጉዳዮች ዲጅታሉን መታወቅያ የማይወስዱ እስከ መጪው ታህሳስ ወር ድረስ የወረቁቱን መታወቂያ እንደሚሰጣቸው ኤጀንሲው ተናግሯል፡፡


ማርታ በቀለ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page