top of page

ሰኔ 13፣ 2016 - በመላው ሀገሪቱ በመጪዎቹ 10 ቀናት ከባድ ዝናብ እንደሚጠበቅ ተነገረ

  • sheger1021fm
  • Jun 20, 2024
  • 1 min read

በመላው ሀገሪቱ በመጪዎቹ 10 ቀናት ከባድ ዝናብ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተናገረ፡፡


ለዝናብ መፈጠር ምክንያት የሚሆኑ የደመና ክምችቶች በመኖራቸው አዲስ አበባን ጨምሮ በመካከለኛና በምዕራብ የሀገራችን ክፍሎች ከበድ ያለ ዝናብ ይጠበቃል ተብሏል፡፡


በአማራ፣ በትግራይ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በአብዛኛው ኦሮሚያ፣ በደቡብ ምዕራብና በምስራቅ የሀገራችን ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚጠበቅ ተጠቁሟል፡፡


ከባድ ዝናብ ይኖራል የተባለባቸውን አካባቢዎችም የነገሩ በኢንስቲትዩቱ በኤጀንሲው የሚቲዎሮሎጂ ትንቤና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ምርምር ዘርፍ ምክትል ሃላፊ የሆኑት ዶክተር አሳምነው ተሾመ ናቸው፡፡


ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በብዙ የሃገራችን አካባቢዎች እየጣለ ያለውና ክረምቱ መጣሁ መጣሁ ማለቱን እያሳየ ያለው ዝናብ ክረምቱን ለሚያመርቱ አካባቢዎች የተመቸ ነውም ብለዋል፡፡


ከባድ ዝናብ ይኖራል በተባሉ አካባቢዎች ያላችሁ ጎርፍ ሊከተል ስለሚችል ጠንቀቅ በሉ ተብላቹሀል፡፡


ምንታምር ፀጋው

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page