top of page

ሰኔ 12፣ 2016 - በህክምና ግብዓት እጥረት ምክንያት፤ ህሙማን ተገቢውን ህክምና ሳያገኙ በረጅም ቀጠሮ ምክንያት ለሞት እየተዳረጉ ነው ተብሏል

  • sheger1021fm
  • Jun 19, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ የካንሰር ህክምና አገልግሎት በብዙ ችግሮች እንደሚፈተን ይነገራል፡፡


ከነዚህም መካከል፤ የህክምና መሳሪያዎችና ሌሎች የህክምና ግብዓቶች አለመኖር ተጠቃሽ ነው፡፡


በህክምና ግብዓት እጥረት ምክንያት፤ ህሙማን ተገቢውን ህክምና ሳያገኙ በረጅም ቀጠሮ ምክንያት ለሞት እየተዳረጉ ነው ተብሏል፡፡


በኢትዮጵያ ከሚከሰቱ የካንሰር አይነቶች መካከል የ30 በመቶውን ድርሻ የሚይዘው የጡት ካንሰር እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡


የማህጸን በር ካንሰር በ13.4 በመቶ እና የትልቁ አንጀት ካንሰር ደግሞ 5.7 በመቶ በመያዝ ይከተላሉ፡፡

ከእነዚህ በተጨማሪ በተለያየ የካነሰር ዓይነቶች የተያዙ ሰዎች በመድሃኒት አለማግኘት፣ በባለሞያ እጥረት፣ በመሳሪያዎች ውስንነት እና በሌሎችም ምክንያቶች እጅጉን እየተቸገሩ እንደሆነ ተነግሯል፡፡


ማርታ በቀለ



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page