top of page

ሰኔ 11፣ 2016 - 73 መስሪያ ቤቶችና 15 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች የመንግስትን የግዢ አዋጅ እና መመሪያ ሳይከተሉ የ2.1 ቢሊየን ብር ግዢ ፈፅመዋል ተባለ

  • sheger1021fm
  • Jun 18, 2024
  • 1 min read

73 መስሪያ ቤቶችና 15 ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች የመንግስትን የግዢ አዋጅ እና መመሪያ ሳይከተሉ የ2.1 ቢሊየን ብር ግዢ ፈፅመዋል ተባለ፡፡


ይህን ያለው የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ነው፡፡


የፌዴራል ዋና ኦዲተር የፌዴራል ዋና መስሪያ ቤት 2015 በጀት ዓመት የፋይናንስ ህጋዊነት ኦዲትና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ለፓርላማው አቅርቧል፡፡


መስሪያ ቤቶቹም በጨረታ መግዛት ሲገባቸው ያለ ጨረታ በቀጥታ የተፈፀመ ግዢ 1.8 ቢሊየን ብር፣ መስፈርቱን ሳያሟላ በውስን ጨረታ የተገዛ ብር 104.3 ሚሊዮን ብር፣ ግልፅ ጨረታ መውጣት ሲገባው በዋጋ ማወዳደሪያ የተፈፀመ ግዢ ብር 96.1 ሚሊየን እና የዋጋ ማወዳደሪያ ሳይሰበሰብ የተፈፀመ ግዢ ብር 13.8 ሚሊየን ግዢ ተፈፅሟል ሲሉ የፌዴራል ዋና ኦዲተሯ መሰረት ዳምጤ ተናግረዋል፡፡


ከደንብና መመሪያ ውጪ ግዢ ከፈፀሙ መሰሪያ ቤቶች መካከል የገቢዎች ሚኒስቴር 1.4 ቢሊየን፣ የኢኖቬሽንና ዜግነት አገልግሎት 91 ሚሊዮን፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 65.5 ሚሊዮን፣ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 62.9 ሚሊዮን ፣ ለኢትዮፕያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ 57.1 ሚሊዮን፣ ቡሌሆራ ዩኒቨርስቲ 34 ሚሊየን ብር ከደንብና መመሪያ ውጪ ግዢ የፈፀሙ መሰሪያ ቤቶች ናቸው ተብሏል፡፡


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page