top of page

ሰኔ 11፣ 2016 - የመንግሥት መስሪያ ቤቶች፤ በመስሪያ ቤቱ ለሌሉና ከስራ ለተሰናበቱ ሰራተኞች ደመወዝ ሲከፍሉ ተገኝተዋል ተባለ

16 የመንግሥት መስሪያ ቤቶች፤ በመስሪያ ቤቱ ለሌሉና ከስራ ለተሰናበቱ ሰራተኞች ደመወዝ ሲከፍሉ ተገኝተዋል ተባለ፡፡


እነዚህ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ለሌሉና ከስራ ለተሰናበቱ ሰራተኞች ብር 485,183.59 ብር ያላግባብ ከፍለው መገኘታቸው ተረጋግጧል፡፡


ይህንን ባደረኩት የኦዲት ሪፖርት አረጋግጫለሁ ያለው የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ነው፡፡

የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ክፍያዎች መመሪያን ተከትለው እንዲፈፀሙ ተገቢው ክትትል ሊደረግ እንደሚገባ ተናግሯል፡፡


ያለአግባብ የተፈጸሙ ክፍያዎችም ተመላሽ መደረግ እንዳለበት በላክሁት ሪፖርት አሳስቤለሁ ብሏል፡፡

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page