ሰኔ 10፣ 2016 - ''ያለ ንግድ ፍቃድ የሚሰሩ፣ ባዕድ ነገሮችን ከምግብ ጋር ቀላቅለው የሚሸጡ ነጋዴዎችን አልታገስም'' የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ
- sheger1021fm
- Jun 17, 2024
- 1 min read
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ከዚህ በኋላ ያለ ንግድ ፍቃድ የሚሰሩትንም ይሁን ባዕድ ነገሮችን ከምግብ ጋር ቀላቅለው የሚሸጡ ነጋዴዎችን አልታገስም አለ፡፡
በአዲስ አበባ ምንም ዓይነት የንግድ ፈቃድ ሳይኖራቸው፤ በየመንደሩ ባለ የንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩትን ለመቆጣጠር መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡
መመሪያው ‘’የመንደር ንግድ ቁጥጥር የአሰራር ሥርዓት’’ በሚል የከተማ አስተዳደሩ ንግድ ቢሮ ሰይሞታል፡፡
በየመንደሩ ያሉ ምንም ዓይነት ፈቃድ ሳይኖራቸው የሚሰሩትን፤ ጥራታቸውን ያልጠበቁና የመጠቀሚ ጊዜያቸው ያለፈባቸውን ምርቶች የሚሸጡ፤ ባዕድ ነገሮችን ከምግብ ጋር ቀላቅለው የሚሸጡ ነጋዴዎችን ለመቆጣጠር ያለመ ነው ተብሏል፡፡
በከተማዋ 400 ሺህ የንግድ ድርጅቶች ፍቃድ አውጥተው እየሰሩ ቢሆንም እዚህም እዚያም፣ በየጥጋ ጥጉ የሚሰሩ ፍቃድ የሌላቸው ነጋዴዎችም ቁጥራቸው ቀላል የሚባል አይደለም፡፡
Comments