top of page

ሰኔ 10፣ 2016 - ''ያለ ንግድ ፍቃድ የሚሰሩ፣ ባዕድ ነገሮችን ከምግብ ጋር ቀላቅለው የሚሸጡ ነጋዴዎችን አልታገስም'' የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ

  • sheger1021fm
  • Jun 17, 2024
  • 1 min read

የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ከዚህ በኋላ ያለ ንግድ ፍቃድ የሚሰሩትንም ይሁን ባዕድ ነገሮችን ከምግብ ጋር ቀላቅለው የሚሸጡ ነጋዴዎችን አልታገስም አለ፡፡


በአዲስ አበባ ምንም ዓይነት የንግድ ፈቃድ ሳይኖራቸው፤ በየመንደሩ ባለ የንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩትን ለመቆጣጠር መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡


መመሪያው ‘’የመንደር ንግድ ቁጥጥር የአሰራር ሥርዓት’’ በሚል የከተማ አስተዳደሩ ንግድ ቢሮ ሰይሞታል፡፡


በየመንደሩ ያሉ ምንም ዓይነት ፈቃድ ሳይኖራቸው የሚሰሩትን፤ ጥራታቸውን ያልጠበቁና የመጠቀሚ ጊዜያቸው ያለፈባቸውን ምርቶች የሚሸጡ፤ ባዕድ ነገሮችን ከምግብ ጋር ቀላቅለው የሚሸጡ ነጋዴዎችን ለመቆጣጠር ያለመ ነው ተብሏል፡፡


በከተማዋ 400 ሺህ የንግድ ድርጅቶች ፍቃድ አውጥተው እየሰሩ ቢሆንም እዚህም እዚያም፣ በየጥጋ ጥጉ የሚሰሩ ፍቃድ የሌላቸው ነጋዴዎችም ቁጥራቸው ቀላል የሚባል አይደለም፡፡



Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡

ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page