top of page

ሰኔ 10፣ 2016 - በርካታ ክልሎች ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ በሆኑ ምክንያቶች ድጋፍ ለሚፈልጉ ሰዎች በራሳቸው ዕርዳታ ማቅረብ ጀምረዋል ተባለ

  • sheger1021fm
  • Jun 17, 2024
  • 1 min read

በርካታ ክልሎች ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ በሆኑ ምክንያቶች ድጋፍ ለሚፈልጉ ሰዎች በራሳቸው ዕርዳታ ማቅረብ ጀምረዋል ተባለ።


የፌዴራል መንግስትን ድጋፍ አሁንም እየፈለጉ ያሉት ብዙ ተረጂዎች ያሉባቸው እና ቅፅበታዊ አደጋ የሚደጋግማቸው ክልሎች እንደሆኑ ሠምተናል።


ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ በሆኑ ምክንያቶች ድጋፍ ለሚፈልጉ ሰዎች ክልሎች በራሳቸው ዕርዳታ የማቅረብ አቅም እንዲፈጥሩ በተለያየ ጊዜ ውይይት ተካሂዶ ከመግባባት መደረሱን፤ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና የኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ አታለለ አቦሃይ ነግረውናል።


በዚሁ መሰረትም አሁን ላይ በርከት ያሉ ክልሎች ድጋፍ ለሚፈልጉ ሰዎች በራሳቸው ዕርዳታ እያቀረቡ ይገኛሉ ብለዋል።


አሁንም የፌዴራል መንግስትን ዕገዛ እየጠየቁ ያሉት ብዙ ድጋፍ ፈላጊዎች ያሉባቸው እና እንደ ትግራይ እና አማራ ያሉ ክልሎች እንደሆኑ ጠቅሰዋል።


ቅጽበታዊ የሆኑ ተፈጥሯዊ አደጋዎች የሚደጋገሙባቸው እንደ አፋር እና ሶማሌ ያሉ ክልሎችም ድጋፍ ፈላጊዎችን ለመርዳት የፌዴራል መንግስትን ዕገዛ እንደሚፈልጉ ሠምተናል።

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page