top of page

ሚያዝያ 7 2017 - ባለፉት 9 ወራት ከ600 ሚሊየን ብር በላይ ከትራፊክ ቅጣት መሰብሰቡን የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣናት ተናገረ።

  • sheger1021fm
  • Apr 15
  • 1 min read

ባለፉት 9 ወራት ከ600 ሚሊየን ብር በላይ ከትራፊክ ቅጣት መሰብሰቡን የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣናት ተናገረ።


ባለስልጣን መ/ቤቱ ባለፉት 9 ወራት ከትራፊክ እና ከመሰል ቅጣቶች በአጠቃላይ ከ700ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ተናግሯል።


በከተማዋ ከሚስተዋለው የትራፊክ ደንብ ጥሰት ውስጥ 40 በመቶው የፍጥነት ወሰን ህግን አለማክበር ነው ተብሏል።

የትራፊክ ቁጥጥሩን ለማዘመን፣ የሙስና ተጋላጭነትን እና የደንብ ጥሰትን ለመቀነስ፣ የተገልጋዮችን እንግልት ለማስቀረት እንዲሁም መሰል የአሰራር ስርአትን ለማሻሻል ዲጂታል አሰራርን እየተገበርኩ ነው ሲል ባለስልጣን መ/ቤቱ ተናግሯል።


የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ክበበው ሚዴቅሳ በትራፊክ ደንብ እና በመሰል ጥሰቶች ቅጣት የምንጥለው ገቢ ለመሰብሰብ ሳይሆን ህግን ለማስከበር ነው ብለዋል።


ፍቅሩ አምባቸው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page