top of page

ሚያዝያ 6 2017 - በየቦታው ገመድ ተወጥሮ የሚጠየቅ የኬላ ክፍያ

  • sheger1021fm
  • Apr 14
  • 1 min read

በየቦታው ገመድ ተወጥሮ የሚጠየቅ የ #ኬላ_ክፍያ ህገ ወጥ ነው መቆምም አለበት፤ ሲል መንግስት በተደጋጋሚ ይናገራል፡፡

ይህን ማድረግ ግን አልተቻለም ተብሏል፡፡


የከባድ ተሽከርካሪ ማህበራት አሽከርካሪዎች በየከተማው በየተወሰነ ኪሎ ሜትሩ ልዩነት ባሉ ኬላዎች በሺዎች የሚቆጠር ብር እንጠየቃለን ብለዋል፡፡


ችግሩ ለሸቀጦች ዋጋ መናር ምክንያት መሆኑም በፓርላማ ጭምር ሲነገር የቆየ ጉዳይ ነው፡፡


በኦሮሚያና በአማራ ክልል አገልግሎት የሚሰጡ አሽከርካሪዎች በየመንገዱ ባሉ የኬላ ክፍያዎች በብርቱ እየተፈተንን ነው ብለዋል፡፡


እነዚህ ህገ ወጥ ክፍያዎችን መንግስት ካስቀመጠው ተመን በላይ እንዲከፍሉ እንደተደረገም አሽከርካሪዎች አስረድቷል፡፡


በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት እና ሶስት ቦታዎች ላይ እንደሚከፍሉም ከአሽከርካሪዎች ሰምተናል፡፡


አላግባብ የሆነ ክፍያ ለምን እንጠየቃለን በምንልበት ወቅት እስከመደብደብ እንደርሳለን ሲሉ ቅሬታቸው ለሸገር ራዲዮ ያቀረቡ አሽከርካሪዎች ይናገራሉ::


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….



ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page