ሚያዝያ 30 2017 - የነዳጅ ክፍያን በኤም-ፔሳ ሳፋሪኮም መክፈል ተጀመረ።
- sheger1021fm
- May 8
- 1 min read
የኤም ፔሳ ሳፋሪኮም ደንበኞች ለመኪናቸው ለሚገዙት ነዳጅ ክፍያ መፈፀም የሚችሉበት የዲጂታል ክፍያ አገልግሎት ትናንት በአዲስ አበባ ቦሌ ቶታል ኢነርጂስ ነዳጅ ማደያ አስጀምሯል።
አገልግሎቱ አሽከርካሪዎች ለነዳጅ ክፍያ በፍጥነት እና ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ የሞባይል ስልኮቻቸውን ተጠቅመው እንዲፈፅሙ ያስችላቸዋል ተብሏል።

በዝግጅቱ ላይ የM-PESA ዋና ስራ አስፈፃሚ ኤልሳ ሙዞሊኒ "ዛሬ በዲጂታል መፍትሄዎች ህይወትን ለማቃለል በምናደርገው ጉዞ ውስጥ ሌላ አስደሳች እርምጃ ተራምደናል ብለዋል።
በኤም ፔሳ ሳፋሪኮም የነዳጅ ክፍያ መፈፀሚያ መላ ለአጠቃቀም ምቹ ሆኖ የቀረበ መሆኑም ተነግሯል።
ይህንን የነዳጅ የክፍያ መላን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ በርኦ ሀሰን እና የኤም ፔሳ ሳፋሪኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ኤልሳ ሙዞሊኒ አስጀምረውታል።
ንጋቱ ሙሉ
コメント