top of page

ሚያዝያ 3 2017 - የመገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት የመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ያወጣውን መግለጫ እንደማይቀበለው ተናግሯል፡፡

  • sheger1021fm
  • Apr 11
  • 1 min read

የመገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ጋዜጠኞችን የመመዝገብና የሙያ ብቃት ማረጋገጫ መታወቂያ እሰጣለሁ ማለቱን ተከትሎ ከትናንት በስቲያ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ባወጣው መግለጫ ስራው የህግ መሰረት የለውም በሚል እውቅና እንደማይሰጠው ተናግሯል፡፡


ተቆጣጣሪ አካል የሆነው ባለስልጣኑ በመግለጫው ምክር ቤቱ ጋዜጠኞችን የመመዝገብም ሆነ የሙያ ማረጋገጫ የመስጠት ሃላፊነት በመገናኛ ብዙሃን አዋጅ አልተሰጠውም ብሏል፡፡


ምክር ቤቱ በበኩሉ አዋጁ ይፈቅድልኛል ባይ ነው፤የምክር ቤቱ ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ ታምራት ሃይሉ በአዋጁ በሚዲያዎችና በጋዜጠኞች መካከል በፍቃደኝነት ላይ የተመሰረተ፤ሙያውን ሊያበረታ የሚችል የእርስ በእርስ ቁጥጥር ስርዓት እንዲኖር እውቅና የሰጠ በመሆኑ ስራውን የጀመርነው፤ የሙያ ማረጋገጫው የሚሰጠው ለሆኑ ፍቃደኛ ለሆኑ የመገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት አባል ለሆኑ ጋዜጠኞች በመሆኑ ከህግ ውጪ አያደርገንም ብለውናል፡፡

በመገናኛ ብዙሃን አዋጁ የሙያ ስነ ምግባርና የመልካም አሰራር ደምብ ማውጣት ይቻላል የሚል የተቀመጠ በመሆኑ፤ ይህንን ለማድረግ ደግሞ ለሙያተኛው ስልጠና ከሰጠን በኋላ የሙያ ብቃት ማረጋገጫውን ለመስጠት እንዳሰቡም በቶ ታምራት ያስረዳሉ፡፡


ባለስልጣኑ ይሁንታውን የማይሰጥ ከሆነ የተጀመረውን ስራ እጣ ፈንታ ምን ይሆናል ላልናቸው የባለልንጣኑን ይሁንታ ባናገኝም ስለ ጉዳዩ እያስረዳን ስራችንን እንቀጥላለን ብለውናል፡፡


ስለ ጉዳዩ ለመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣኑ ስለ ጉዳዩ ቀድመን አሳውቀን ነበር፤ በጋራ የምንሰራቸው ስራዎች አሉ፤በሚቀጥለው ሳምንት ስለ ጉዳዩ ለመነጋገር ቀጠሮ ይዘናል ብለዋል፡፡


የመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንን ስለ ጉዳዩ ማብራሪያ የጠየቅን ቢሆንም ባለስልጣኑ በመግለጫው ከጠቀሰው ውጪ ማብራሪያ እንደማይሰጥ ነግሮናል።


ምንታምር ፀጋው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page