ሚያዝያ 29 2017 - በቴክኒክና ሞያ ተቋማት ውስጥ ክህሎት ያለው የመምህር እጥረት ከፍተኛ መሆኑን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ያደረገው ጥናት አሳየ፡፡
- sheger1021fm
- May 7
- 1 min read
በቴክኒክና ሞያ ተቋማት ውስጥ ክህሎት ያለው የመምህር እጥረት ከፍተኛ መሆኑን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ያደረገው ጥናት አሳየ፡፡
በተለይም ከዩኒቨርሲቲ ተመርቀው በቴክኒክና ሞያ የሚያስተምሩ መምህራን በኢንዱስትሪዎች የመስራት ልምድ ስለሌላቸው በሞያው የክህሎት እጥረት እንደሚታይባቸው ጥናቱ ጠቅሷል፡፡
የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ‘’የቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ስልጠና ሥርዓት ግንባታ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ሽግግር’’ በሚል ርዕስ ነው ጥናቱን ያደረገው፡፡
በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት መሪ ተመራማሪ የሆኑት እና በዚህ ጥናት ከተሳተፉ ባለሞያዎች መካከል አማረ ማተቡ(ዶ/ር) አንዱ ናቸው፡፡
ከቴክኒክና ሞያ ሰልጥነው የሚወጡ ባለሞያዎች የክህሎት ማነስ እንደሚታይባቸው አምራች ተቋማት ነግረውናል ብለዋል፡፡
ከዚህ ባለፈም በዘርፉ ተሰማርተው ከሚያስተምሩ መምህራን መካከል የተግባር ተኮር የስራ ልምድ የሌላቸው መምህራን አሉ የተባለ ሲሆን ይህም ክህሎትና ጥራት ያለው ሰልጣኝ ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ላይ ዋንኛ ችግር መሆኑን ዶክተር አማረ ነግረውናል፡፡
ከዚህም ባለፈ በቴክኒክና ሞያ ተቋማት ለተግባር መማሪያ ተብለው የተገዙ ቁሳቁሶች ዘመኑ እየሄበት ካለው ቴክኖሎጂዎች ጋር የሚጣጣም አይደለም ይህም ሰልጣኙ ወደ ስራው አለም ሲገባ አዲሱን ቴክኖሎጂ ለመላመድ እንዲቸገር እንደሚያደርገው ጥናቱ ያስረዳል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..
በረከት አካሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r












Comments