ሚያዝያ 16 2017 - ተማሪዎች ከ2018 ጀምሮ ት/ቤት ስልክ ይዘው እንዳይገቡ ይደረጋል መባሉ ት/ቤቶችና መምህራን እንዴት ያዩታል?
- sheger1021fm
- Apr 24
- 1 min read
ትምህርት ሚኒስቴር ተማሪዎች ከ2018 ጀምሮ ትምህርት ቤት ውስጥ #ስልክ ይዘው እንዳይገቡ የሚያደርግ ህግ ሊተገብር ማቀዱን ተናግሯል፡፡
ህጉን ወደ መሬት ለማውረድ ትምህርት ሚኒስቴር ከዘርፉ አመራሮች ጋር፤ እንደ ሀገር ወጥ የሆነ መግባባት ላይ ለመድረስ ውይይት ለማድረግ እቅድ መያዙን ሰምተናል፡፡
ታዲያ ህጉ ትምህርት ቤቶች እንዴት ያዩታል? መምህራን በዚህ ዙሪያ ምን ሃሳብ አላቸው ብለን ጠይቀናል፡፡
ተማሪዎች አሁን ላይ ክፍል ውስጥ ስልክ ይዘው ሲማሩ ‘’ትምህርት ከመከታተል ይልቅ ማህበራዊ ትስስር ገፅ ነው የሚጠቀሙት’’ የሚሉ እንዳሉ ሁሉ ‘’የመፅሀፍት እጥረትን ተከትሎ አንዳንድ ተማሪዎች ስልካቸውን በመጠቀም የተለያዩ አጋዥ መፅሀፍትን ከተለያዩ ድህረ ገፆች በማውረድ የሚያነቡ አሉ’’ የሚል ሀሳብ ያላቸውም አሉ፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
በረከት አካሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r
Comments